Popular Posts

Thursday, March 7, 2019

እግዚአብሔርም ቤት ይፈልጋል !

እግዚአብሔርም ቤት ይፈልጋል !
ኢየሱስም መለሰ አለውም፦ የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል ወደ እርሱም እንመጣለን በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን። የዮሐንስ ወንጌል 14፡23
ሰው በተፈጥሮው ቤቴ የሚለው ማረፊያ ቦታ ይፈልጋል፡፡ ሰው ከዚያ እየተነሳ የሚሰራበት የሚማርበት የሚንቀሳቀስበት መነሻ ቤት ይፈልጋል፡፡ ሰው ሰዎች ሌሎች ሰዎች ሲፈልጉት የሚገኝበት እንግዳውን የሚቀበልበት የሚያስተናግድበት ቤት ይፈልጋል፡፡
እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው ለእርሱ ማረፊያ መኖሪያ ቤት እንዲሆን ነው፡፡
እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው የሚናከትረብት መድረክ እንዲሆንለት ነው፡፡
እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው መልካምነቱን የሚያሳይበት ቦታ እንዲሆንለት ነው፡፡
እግዚአብሄር ሰው በሰራው ቦታ ውስጥ አይኖርንም፡፡ እግዚአብሄር ደስ ብሎት የሚያርፈው እና የሚኖረው ራሱ በሰራውና በፈጠረው ሰው ውስጥ ነው፡፡
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ ሰማይ ዙፋኔ ነው፥ ምድርም የእግሬ መረገጫ ናት፤ የምትሠሩልኝ ቤት ምን ዓይነት ነው? የማርፍበትስ ስፍራ ምንድር ነው? እነዚህን ሁሉ እጄ ሠርታለችና እነዚህ ሁሉ የእኔ ናቸው፥ ይላል እግዚአብሔር፤ ነገር ግን ወደዚህ ወደ ትሑት፥ መንፈሱም ወደ ተሰበረ፥ በቃሌም ወደሚንቀጠቀጥ ሰው እመለከታለሁ። ትንቢተ ኢሳይያስ 66፡1-2
ሰው በተፈጥሮው ንፁህ ቤት ውስጥ መኖር እንደሚፈልግ ሁሉ እግዚአብሄርም የሚኖርበት ንፁህ ቤት ንፁህ ህይወት እንዲሆንለት ይፈልጋል፡፡ 
ወይስ ሥጋችሁ ከእግዚአብሔር የተቀበላችሁት በእናንተ የሚኖረው የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ እንደ ሆነ አታውቁምን? በዋጋ ተገዝታችኋልና ለራሳችሁ አይደላችሁም፤ ስለዚህ በሥጋችሁ እግዚአብሔርን አክብሩ። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6፡19-20
መፅሃፍ ቅዱስ ለእግዚአብሄር መኖሪያ ሆናችሁ ተሰሩ በማለት ያዘናል፡፡
እናንተ ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠሩ። 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 2፡5
ባደግን ፣ በሰፋንና በነፃን መጠን ለእግዚአብሄር ይበልጥ የሚመች መኖሪያና ማገልገያ ቤት ሆን እንሰራለን፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ትህትና #የእግዚአብሔርቤት #በቃሉመንቀጥቀጥ #ማረፊያ #መኖሪያ #የተሰበረልብ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ማደሪያ #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  #የዋህነት #ንፁህ

No comments:

Post a Comment