Popular Posts

Monday, March 4, 2019

ለመውደድና ለመወደድ

ሰው ለመውደድና ለመወደድ ፍቅር በሆነው በእግዚአብሄር ተፈጥሮአል፡፡ ሰው ካልወደደና ካልወደደ የተፈጠረበትን አላማ ስቷል ማለት ነው፡፡
እኛም እግዚአብሔር ለእኛ ያለውን ፍቅር አውቀናል አምነንማል። እግዚአብሔር ፍቅር ነው፥ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል። 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4፡16
ሰው ሲፈጠር ለሌላው ሰው ከሚያካፍለው መልካም ስጦታ ጋር ተፈጥሮአል፡፡ በሰው ውስጥ ያለው ነገር ለሌላው ሰው የሚጠቅም ነገር ነው፡፡
ሰው ያለምክኒያት ለመውደድ ዲዛይን ተደርጎ ስለተፈጠረ ሰው ሌላውን ካልወደደ ፣ በውስጡ ባለው ነገር ሌላውን ካልጠቀመና ካላገለገለ የተፈጠረበትን አላማ ይስታል፡፡
በተሰጠንም በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን ስለ ፈሰሰ ተስፋ አያሳፍርም። ወደ ሮሜ ሰዎች 5፡5
ሰው ሌላውን ለመውደድ ብቻ ሳይሆን ለመወደድም ደግሞ ተፈጥሮአል፡፡ ሰው እርሱን የሚወደውና የሚፈልገው ሰው ይፈልጋል፡፡ ሰው ሲፈጠር ከከበረ ነገር ጋር ስለተፈጠረ ያለውን የከበረ ነገር እውቅና የሚሰጠው ሰው ይፈልጋል፡፡ ሰው አስፈላጊነቱንና ጠቃሚነቱን እውቅና የሚሰጠውን ሰው ይፈልጋል፡፡ ሰው ህይወቱ ለሌላው ሰው አስፈላጊ እንደሆነ ማወቅ ይፈልጋል፡፡ ሰው መፈለግ መወደድ ይፈልጋል፡፡     
ሰው ህይወቱ ለሌሎች የሚጠቅም ትርጉም ያለው ህይወት እንዲሆን ይፈልጋል፡፡ ሰው ህይወቱ ለሌሎች የሚጠቅም አስፈላጊ እንደሆነ ማወቅ ይፈልጋል፡፡ ሰው ለሌላው ጠቃሚና አስፈላጊ እንደሆነ ካላወቀ የህይወት ጣእሙን ያጣዋል፡፡
ሰው በእግዚአብሄር እንደተወደደ ካወቀ በሌላ በማንም ሰው ሊወደድ እንደሚችል ማመን አያቅተውም፡፡ ሰው በእግዚአብሄር እንደተወደደ ካወቅ የመወደድ ፍላጎቱ ይረካል፡፡ ሰው በእግዚአብሄር እንደተወደደ ማወቁ ብቻ በሰው ያለመወደዱን ፈተና ተቋቁሞ እንዲያልፍ ይረዳዋል፡፡ በምድር ላይ መኖሩ ለእግዚአብሄር ትርጉም እንዳለው ካወቀ ሰው በምድር ላይ መኖሩ ለሌላው ሰው ትርጉም እንዳለው ማወቅ አያቅተውም፡፡
እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ፥ እንደ ወደድኋችሁ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ አዲስ ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ። የዮሐንስ ወንጌል 13፡34
ሰው በእግዚአብሄር እንደተወደደ ካወቀ ሌላውን ለመውደድ ፣ ለመጥቀምና ለማገልገል አቅም ያገኛል፡፡ የሰው ህይወቱ ትርጉም የሚያገኘው በእግዚአብሄርና በሰው መወደዱን ሲረዳና እግዚአብሄርን እና ሰውን ሲወድ ነው፡፡ 
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ፍቅር #መውደድ #መወደድ #ማስተዋል #እግዚአብሔርንመፍራት #ጥበብ #ክፉ #መልካም #መጥቀም #እውቅና #ፍፁም #ማገልገል #መፍትሄ #አላማ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ  #እምነት #ቃል  #ማደስ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment