Popular Posts

Sunday, June 16, 2019

ስምንቱ የአባቶች ቀን ውሳኔዎች


1.      ልጆቼን ልመክርና ልገስፅ ግን ላላቆጣ እወስናለሁ
እናንተም አባቶች ሆይ፥ ልጆቻችሁን በጌታ ምክርና በተግሣጽ አሳድጉአቸው እንጂ አታስቆጡአቸው። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6፡4
2.     ለልጆቼ በእግዚአብሄር ቃል ምሳሌ ለመሆን እወስናለሁ
ባገኘሁት ጊዜ ሁሉ የስጋ ልጆቼ ላልሆኑት የአባትነትን ምክርና እንክብካቤ እሰጣለሁ፡፡
3.     ልጆቼን የእግዚአብሄርን መንገድ ለማሳየት ለማስተማር እወስናለሁ፡፡
ልጅን በሚሄድበት መንገድ ምራው፥ በሸመገለም ጊዜ ከእርሱ ፈቀቅ አይልም። መጽሐፈ ምሳሌ 22፡6
4.     ለቤተሰቤ የሚያስፈልገውን ደከመኝ ሰለቸኝ ሳልል በመትጋት ለማቅረብ  እወስናለሁ፡፡
ነገር ግን ለእርሱ ስለ ሆኑት ይልቁንም ስለ ቤተ ሰዎቹ የማያስብ ማንም ቢሆን፥ ሃይማኖትን የካደ ከማያምንም ሰው ይልቅ የሚከፋ ነው። 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 5፡8
5.     አባት ለሌለው ለድሃ አደጉ የመፍረድና የመከራከር መልካም ስራ በትጋት ለመስራት እወስናለሁ፡፡
መልካም መሥራትን ተማሩ፥ ፍርድን ፈልጉ፥ የተገፋውን አድኑ፥ ለድሀ አደጉ ፍረዱለት ስለ መበለቲቱም ተምዋገቱ። ትንቢተ ኢሳይያስ 1፡17
6.     የቤተሰቡን ችግር ከፊት ሆኜ ልጋፈጥ ችግሩ ወደ ቤተሰቤ እንዳይመጣ ቤተሰቤን ልከላከልና ጥላ ልሆናቸው እውስናለሁ፡፡
አባት ለልጆቹ እንደሚራራ እንዲሁ እግዚአብሔር ለሚፈሩት ይራራል፤ መዝሙረ ዳዊት 103፡13
7.     በማንኛውም ሁኔታ ቤተሰቤን ላፅናና እና ላበረታታ እወስናለሁ፡፡
የርኅራኄ አባት የመጽናናትም ሁሉ አምላክ የሆነ የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክና አባት ይባረክ። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 1፡3
8.     በስጋ ልጄ ላልሆነ በተለይ ይህ የአባትነት እድል ለማያገኘው በየትም ስፍራ ለማገኘው ልጅ በቻልኩት መጠን ሁሉ የአባትነት ተምሳሌ ልሆነው በህይወቱ ላይ አንድ የማበረታቻ ቃል አንኳን ቢሆን የአባትነትን አስተዋፅኦ ለማድረግ እወስናለሁ፡፡   
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
መልካም የአባቶች ቀን!
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ወላጅ #ፍቅር #አባት #እርማት #ጥንካሬ #ራእይ #ደረጃመስጠት #ጥላ #ማበረታታት #አባትነት #ተግሳፅ  #መሪ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #ቸርነት #ትግስት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment