ልናጣው የማንችለው ነገር ሁሉ የእኛ አይደለም
በህይወታችን ዘመን ብዙ በረከቶች ወደ ህይወታችን ይመጣሉ:: እኛን ለመባረክና እና ለመጥቀም እግዚአብሔር ልዩ ልዩ መንገዶችን ይጠቀማል:: በህይወታችን ያለውን አላማውን ለመፈጸም እግዚአብሄር በብዙ አይነት እና በብዙ መንገድ የሚጠቀምባቸው ነገሮች ሁሉ የጊዜው ናቸው እንጂ ለዘላለም አይደሉም::
ከእግዚአብሔር ውጭ ምንም ቋሚ ነገር የለም:: ከእግዚአብሔር ውጭ የሚታየው ነገር ሁሉ ሃላፊ ነው::
ቋሚ ያልሆነን ነገር እንደ ጊዜያዊነቱ በትክክል መያዝ ከብዙ ጭንቀት ያድናል::
ከእግዚአብሔር ውጭ ይህን ካላገኘሁ አልኖርም የምንለው ምንም ነገር መኖር የለበትም::
እግዚአብሔር የሚሰጠንን ነገሮች ጨምሮ አንድ ቀን እንደማንለያቸው አድርገን ውስጣችን ማስገባት ችግርን መጋበዝ ነው:: የራሳችንን ማንነትና ነፃነት እስከምናጣ ድረስ ሁኔታዎችን ውስጣችን መክተት ጊዜያዊዉን ነገር ስንለየው ስቃይ ውስጥ መግባት ያስገባናል:: የነገሮችን ጊዜያዊነትና ልካቸውን ማወቅ ብልህነት ነው፡፡ ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ የሚለውን ቃል መከትል ጥበብ ነው::
አንተ ግን ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ፥ መከራን ተቀበል፥ የወንጌል ሰባኪነትን ሥራ አድርግ፥ አገልግሎትህን ፈጽም። 2ኛ ጢሞቴዎስ 4:5
ለዘላለም ከሚኖረው ከእግዚአብሔር ቃል ውጭ ሁኔታዎችን ወደ ውስጣችን አለማስገባትና በውጭ መጠበቅ ስንለይ ከሚመጣ የመለያየት ስቃይ ይጠብቀናል::
የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ . . . የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው። 2ኛ ቆሮንቶስ 4:17-18
ብዙ ጊዜ ሰይጣን የሚያስፈራራንና እስራት ውስጥ የሚከተን ይህን ነገር ብታጣውስ ብሎ በማስፈራራት ነው:: እግዚአብሔርን አልጣው እንጂ ካለእርሱ መኖር የማልችለው ምንም ነገር የለም ካልን ለሰይጣን እድል ፈንታ አንሰጠውም:: ከእግዚአብሔር ውጭ ካለእርሱ መኖር አልችልም የምንለው ነገር ካለ በዘመናችን ሁሉ በፍርሃት ባርነት ውስጥ እንቆያለን ::
ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4፡27
በምንም ነገር በእውነት ተጠቃሚ የምንሆነው ላጣው አልችልም ብለን የምናስበውን ነገር ከሌለና ማንኛውንም ነገር ለማጣት ከተዘጋጀን ብቻ ነው::
ይህን ካጣኽው መኖር አትችልም የሚለው በፅኑ ልንቃወመው የሚገባ የሰይጣን ድምፅ ነው::
ልንይዘውና ልንጠቀምብት እንጂ ምንም ነገር ሊይዘን እና ሊቆጣጠረን አይገባም::
ዳሩ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እናገራለሁ፤ ዘመኑ አጭር ሆኖአል፤ ከእንግዲህ ወዲህ ሚስቶች ያሉአቸው እንደሌላቸው ይሁኑ፥ የሚያለቅሱም እንደማያለቅሱ፥ ደስ የሚላቸውም ደስ እንደማይላቸው፥ የሚገዙም ምንም እንደሌላቸው፥ በዚችም ዓለም የሚጠቀሙ በሙሉ እንደማይጠቀሙባት ይሁኑ፤ የዚች ዓለም መልክ አላፊ ነውና። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 7፡29-31
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #የእግዚአብሄርፈቃድ #ፀሎት #ልመና #ምልጃ #ምስጋና #ውዳሴ #በመጠኑ #እንደፈቃዱ #መጠየቅ #መንበርከክ #ይቃትታል #መንፈስቅዱስ #እንዲሰማን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #የእግዚአብሄርቃል #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
በአለማችን ላይ እውነተኛ ደቀመዛሙርቶች አሉ፡፡ የስም ብቻ ደቀመዛሙርቶች ደግሞ አሉ፡፡ እውነተኛ ደቀመዝሙር የሚያደርገን ምን እንደሆነ ማወቅ በጣም ወሳኝ ነገር ነው፡፡ የእውነተኛ ደቀመዝሙርነት መንገድ ላይ መሆናችንን ...
-
እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር ፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ...
-
https://youtu.be/VhF0pSsp14I በቃልኪዳን መነጽር ህይወታችን ማየት አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa ሬማ እምነት አገልግሎት በርሚንግሃም ቤተክርስትያን
-
Live soberly and be vigilant, for the devil, who is not your partner, prowls around like a roaring lion looking for someone to devour. Re...
-
ነቢይ የእግዚአብሄር አፍ ነው፡፡ ነቢይ ከለአግዚአብሄር ሰምቶ የሚናገር ነው፡፡ ነቢይ የእግዚእብህር በልቡና ያለውን ተረድቶ ለህዝቡ የሚገልፅ ነው፡፡ በድሮ ዘመን ብቻ ሳይሆን እግዚአብሄር ነቢይን በዚህ በእኛ ዘመን ...
-
ተጠማው እልውናህን መገኘትህን ጌታ ድምጽህን መዓዛ ግርማህን አልፈልግም ኖረ ኖረ ኖረ ሞተ አልፈልግም መሆን በምድር የታመነ መንፈስክን ይዞ ይዞ ሚገሰግስ ለተጠማው ደርሶ የልብህን የሚያደር...
-
Bait your hook an' keep a- tryin '-- Keep a-goin '! When the weather kills your crop, Keep a-goin '! Though 'tis...
-
የወርቅ ቀለበት በእርያ አፍንጫ እንደ ሆነ፥ ከጥበብ የተለየች ቆንጆ ሴትም እንዲሁ ናት። መጽሐፈ ምሳሌ 11፡22 የኛውም ወርቅ እርያን አንደማያሳምረው ሁሉ የትኛውም የውጭ ውበት የውስጡን ሰውን አያ...
-
እናንተ ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠ...
-
በነጻነት ሕግ ፍርድን ይቀበሉ ዘንድ እንዳላቸው ሰዎች እንዲህ ተናገሩ፥ እንዲህም አድርጉ። የያዕቆብ መልእክት 2፡ 12 በክርስቶስ ከሃጢያት እስራትና ፍርድ ነፃ ወጥተናል፡፡ ነገር ግን ነፃነት የሚመጣ...

No comments:
Post a Comment