ልናጣው የማንችለው ነገር ሁሉ የእኛ አይደለም
በህይወታችን ዘመን ብዙ በረከቶች ወደ ህይወታችን ይመጣሉ:: እኛን ለመባረክና እና ለመጥቀም እግዚአብሔር ልዩ ልዩ መንገዶችን ይጠቀማል:: በህይወታችን ያለውን አላማውን ለመፈጸም እግዚአብሄር በብዙ አይነት እና በብዙ መንገድ የሚጠቀምባቸው ነገሮች ሁሉ የጊዜው ናቸው እንጂ ለዘላለም አይደሉም::
ከእግዚአብሔር ውጭ ምንም ቋሚ ነገር የለም:: ከእግዚአብሔር ውጭ የሚታየው ነገር ሁሉ ሃላፊ ነው::
ቋሚ ያልሆነን ነገር እንደ ጊዜያዊነቱ በትክክል መያዝ ከብዙ ጭንቀት ያድናል::
ከእግዚአብሔር ውጭ ይህን ካላገኘሁ አልኖርም የምንለው ምንም ነገር መኖር የለበትም::
እግዚአብሔር የሚሰጠንን ነገሮች ጨምሮ አንድ ቀን እንደማንለያቸው አድርገን ውስጣችን ማስገባት ችግርን መጋበዝ ነው:: የራሳችንን ማንነትና ነፃነት እስከምናጣ ድረስ ሁኔታዎችን ውስጣችን መክተት ጊዜያዊዉን ነገር ስንለየው ስቃይ ውስጥ መግባት ያስገባናል:: የነገሮችን ጊዜያዊነትና ልካቸውን ማወቅ ብልህነት ነው፡፡ ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ የሚለውን ቃል መከትል ጥበብ ነው::
አንተ ግን ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ፥ መከራን ተቀበል፥ የወንጌል ሰባኪነትን ሥራ አድርግ፥ አገልግሎትህን ፈጽም። 2ኛ ጢሞቴዎስ 4:5
ለዘላለም ከሚኖረው ከእግዚአብሔር ቃል ውጭ ሁኔታዎችን ወደ ውስጣችን አለማስገባትና በውጭ መጠበቅ ስንለይ ከሚመጣ የመለያየት ስቃይ ይጠብቀናል::
የማይታየውን እንጂ የሚታየውን ባንመለከት፥ . . . የሚታየው የጊዜው ነውና፥ የማይታየው ግን የዘላለም ነው። 2ኛ ቆሮንቶስ 4:17-18
ብዙ ጊዜ ሰይጣን የሚያስፈራራንና እስራት ውስጥ የሚከተን ይህን ነገር ብታጣውስ ብሎ በማስፈራራት ነው:: እግዚአብሔርን አልጣው እንጂ ካለእርሱ መኖር የማልችለው ምንም ነገር የለም ካልን ለሰይጣን እድል ፈንታ አንሰጠውም:: ከእግዚአብሔር ውጭ ካለእርሱ መኖር አልችልም የምንለው ነገር ካለ በዘመናችን ሁሉ በፍርሃት ባርነት ውስጥ እንቆያለን ::
ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 4፡27
በምንም ነገር በእውነት ተጠቃሚ የምንሆነው ላጣው አልችልም ብለን የምናስበውን ነገር ከሌለና ማንኛውንም ነገር ለማጣት ከተዘጋጀን ብቻ ነው::
ይህን ካጣኽው መኖር አትችልም የሚለው በፅኑ ልንቃወመው የሚገባ የሰይጣን ድምፅ ነው::
ልንይዘውና ልንጠቀምብት እንጂ ምንም ነገር ሊይዘን እና ሊቆጣጠረን አይገባም::
ዳሩ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እናገራለሁ፤ ዘመኑ አጭር ሆኖአል፤ ከእንግዲህ ወዲህ ሚስቶች ያሉአቸው እንደሌላቸው ይሁኑ፥ የሚያለቅሱም እንደማያለቅሱ፥ ደስ የሚላቸውም ደስ እንደማይላቸው፥ የሚገዙም ምንም እንደሌላቸው፥ በዚችም ዓለም የሚጠቀሙ በሙሉ እንደማይጠቀሙባት ይሁኑ፤ የዚች ዓለም መልክ አላፊ ነውና። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 7፡29-31
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #የእግዚአብሄርፈቃድ #ፀሎት #ልመና #ምልጃ #ምስጋና #ውዳሴ #በመጠኑ #እንደፈቃዱ #መጠየቅ #መንበርከክ #ይቃትታል #መንፈስቅዱስ #እንዲሰማን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #የእግዚአብሄርቃል #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ
I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
በክርስትና ለቤተክርስቶን ከተሰጡ አገልግሎቶች መካከል ትንቢት አንዱ ነው፡፡ ትንቢት የሚመጣው ለማነጽና ለመምከር ለማጽናናትም ነው፡፡ ትንቢትን የሚናገር ግን ለማነጽና ለመምከር ለማጽናናትም ለሰው ይናገራል። 1...
-
Then Peter opened his mouth, and said, Of a truth I perceive that God is no respecter of persons: Acts 10:34 God isn’t a respecter...
-
We all come across disappointments. We may face situations that we have never dreamed of facing them one day. We may face something we t...
-
እንደ ፍቅር በጣም አስፈላጊ ነገር የለም፡፡ እንደ ፍቅር ደግሞ ትርጉሙ የተዛባ ነገር በአለም ላይ ምንም ነገር የለም፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች ፍቅር የሚሉት ምኞታቸውን ነው፡፡ የፍቅርንና የምኞትን ባህሪያት ከእግዚአብሄር ቃ...
-
እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው ከእርሱ ጋር ህብረት ማድረግ ፈልጎ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን በመልኩና በአምሳሉ የፈጠረው ህብረታቸው የተሳካ እንዲሆን ነው፡፡ ሰው በሃጢያት ከመውደቁ በፊት ከእግዚአብሄ ጋር የተሳካ ህብ...
-
ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥ አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ፦ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድን...
-
ማሪያም ታማልዳለች ወይስ አታማልድም የሚለው ጥያቄ በኢትዮጲያ ውስጥ ብዙ ክርክርን ሲያስነሳ የቆየ ጥያቄ ነው፡፡ አንዳንዶች ማሪያም በምድር ላይ እያለች አማልዳለች ነገር ግን ከሞተች በኃላ ማማለድ አትችልም ብለው...
-
We want God to use us mightily. We ask God “use me and I will do whatever it takes”. When the time to pay the price that isn’t expected...
-
መንፈስ ይሙላባችሁ እንጂ በወይን ጠጅ አትስከሩ ይህ ማባከን ነውና፤ ኤፌሶን 5፡18 የእግዚአብሄርን ነገር በመንፈስ ነው የሚሰራው፡፡ የተለያዩ ሃይማኖታዊ እንቅስቃሴዎችን ማድረግ እንችላለን ካለ መንፈስ ሙላትና እ...
-
ሰዎችን የሚማርኳቸውና የሚደሰቱባቸው ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ ካለ እምነት ግን እግዚአብሄርን ደስ ማሰኘት አይቻልም፡፡ ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ ...

No comments:
Post a Comment