Popular Posts

Sunday, June 23, 2019

ቸሩ እግዚአብሔር



እግዚአብሄር አይለወጥም የእግዚአብሄር መልካምነት አይለወጥም
እግዚአብሄር ሁሌ መልካም ነው፡፡ የእግዚአብሄር መልካምነት ባህሪው ነው፡፡ እግዚአብሄርን ብታገላብጡት መልካም እንጂ ክፉ ሊሆን አይችልም፡፡
የተወደዳችሁ ወንድሞቼ ሆይ፥ አትሳቱ። በጎ ስጦታ ሁሉ ፍጹምም በረከት ሁሉ ከላይ ናቸው፥ መለወጥም በእርሱ ዘንድ ከሌለ በመዞርም የተደረገ ጥላ በእርሱ ዘንድ ከሌለ ከብርሃናት አባት ይወርዳሉ።  የያዕቆብ መልእክት 1፡16-17
እግዚአብሄር ከምድር አባት ሁሉ የሚበልጥ ልዩ አባት ነው
አብልጦ መልካም ነገርን ይሰጣል፡፡
ይህ ከምድር ኣበቶች ሁሉ በአባትነቱ መልካምነት የሚበልጠው እግዚአብሄር በክርስቶስ ኢየሱስ አዳኝነት ላመንን ሁላችን አባታችን ሆኖዋል፡፡  
ወይስ ከእናንተ፥ ልጁ እንጀራ ቢለምነው፥ ድንጋይን የሚሰጠው ከእናንተ ማን ሰው ነው? ዓሣስ ቢለምነው እባብን ይሰጠዋልን? እንኪያስ እናንተ ክፉዎች ስትሆኑ ለልጆቻችሁ መልካም ስጦታ መስጠትን ካወቃችሁ፥ በሰማያት ያለው አባታችሁ ለሚለምኑት እንዴት አብልጦ መልካም ነገርን ይሰጣቸው? የማቴዎስ ወንጌል 7፡9-11
እግዚአብሄር የመልካምነት ማጣቀሻ ነው፡፡
ስለአንድ መልካምነት ክርክር ከተነሳ ውሳኔውን የሚሰጥ እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡ መልካም የሚባለው እግዚአብሄር መልካም ካለው ነው፡፡ ክፉ የሚባለው እግዚአብሄር  በቃሉ ክፉ ካለው ብቻ ነው፡፡ የመልካምነት ደረጃ መዳቢ እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡  
የእግዚአብሄር መልካምነት በወሳኝ ጊዜ ይታያል
ብዙ መልካም ሊያደርጉልን የሚፈልጉ በመካከላችን አሉ፡፡ ነገር ግን ሁሉም በማይችሉበት ጊዜ ምላምን ከሊያደርግልን የሚችል እግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል። ትንቢተ ናሆም 1፡7
የትኛውም መልካምነት የሚመነጨው ከእግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
እናንትም ምንም መልካም ማድረግ ብትፈልጉ እግዚአብሄር ካልተጠቀመባችሁ ለማንም አትጠቅሙም፡፡
እግዚአብሔርን፦ አንተ ጌታዬ ነህ አልሁ፤ ከአንተ በቀር በጎነት የለኝም። መዝሙረ ዳዊት 16፡2
ሰው ምንም ቢያዝናችሁ ሃዘናችሁን ይካፈላል እንጂ እግዚአብሄር ካልተጠቀመበት ምንም መልካምነት ሊያደርግላችሁ አይችልም፡፡  
ኢየሱስም፦ ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም። የሉቃስ ወንጌል 18፡19
እግዚአብሄር ለእኛ የሚያስብ ፍፁም አሳብ ያለው መልካም አባት ነው፡፡
ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም። ትንቢተ ኤርምያስ 29፡11
ስለዚህ እግዚአብሄርን ማመስገን መልካም ነው፡፡ እግዚአብሄርን ባለማመስገን እንጂ እግዚአብሄርን አመስግኖ የሚሳሳት ሰው የለም፡፡ እግዚአብሄር መልካም ነው፡፡
ሃሌ ሉያ። ቸር ነውና፥ ምሕረቱ ለዘላለም ነውና እግዚአብሔርን አመስግኑ፤ መዝሙረ ዳዊት 107፡1
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ማካፈል share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #አመስግኑ #መልካም #እምነት #ቃልኪዳን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #የዘላለምህይወት #ቸር #መንፈስ #መንፈስቅዱስ

No comments:

Post a Comment