Popular Posts

Wednesday, June 12, 2019

አትሳቱ


አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል። 1 ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15፡33
የእግዚአብሔርን ህግ መከተል ከህመም ያሳርፋል፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ማዳማጥ እግዚአብሄርን ለህይወታችን ያለውን ፈቃዱን ከመሳት ያድናል፡፡ ለእግዚአብሄር ቃል የዋህ መሆን ከብዙ ጥፋት ያድናል፡፡
ከእግዚአብሄር በላይ ያወቅን ሲመስለን ራሳችንን እንጎዳለን፡፡ ለእግዚአብሄር ትእዛዝ ቸልተኞች ስንሆን የማይገባንን ዋጋ እንከፍላለን፡፡
መፅሃፍ ቅዱስ አትሳቱ ይላል፡፡ መፅሃፍ ቅዱስ አይምሰላችሁ ይለናል፡፡ መፅሃፍ ቅዱስ አትሸወዱ ብሎ በብርቱ ይመክረናል፡፡
መፅሃፍ ቅዱስ አትሳቱ ያለበት ምክኒያት ይህ ነገር ሰው ብዙ ሰው ብዙ ጊዜ የሚሳሳትበት ነገር ስለሆነ ነው፡፡ ሰው ብዙ ጊዜ ከሆነው በላይ ጠንካራ የሆነ ይመስለዋል፡፡ ሰው ብዙ ጊዜ ከሆነው በላይ ጠቢብ እንደሆነ ሲመስለው ይሸወዳል፡፡
እግዚአብሄር አዋቂ ነው፡፡ ሰው እግዚአብሄር አታድርግ ያለውን አድርጎ በሰላም እንደሚኖር ካሰበ ሞኝ ሆኖዋል፡፡ ሰው እግዚአብሄር ተው ያለውን ሳይተው እንደማይወድቅ ካሰበ ተታሏል፡፡
እግዚአብሄር አትሳቱ ይለናል፡፡ በምን ብለን መጠየቅ እና ትእዛዙን በፍጥነት ለመጠበቅ እርምጃ መውሰድ ብልህነት ነው፡፡
እግዚአብሄር በተለይ በክፉ ባልነጀርነት አትሳቱ ብሎ ይመክረናል ያስጠነቅቀናል፡፡ ክፉ ባልንጀራ ይዞ ክፉ አልሆንም የሚል ሰው ለራሱ ከሚገባው በላይ ግምት እየሰጠ ነው፡፡ ክፉ ባልንጀነት ይዞ አልስትም ማለት በከንቱ በራስ መመካት ነው፡፡ የክፉ ባልንጀርነት ውጤት እኔን አይነካኝም ብሎ ማሰብ ትእቢት ነው፡፡
ወደድንም ጠላንም ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል፡፡ በክፉ ባልንጀርነት ቆይተን አለን ያልነው መልካም አመል  ቢጠፋ አንደነቅ፡፡ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ይበላል፡፡
ስለምድራዊ ህይወት ብቻ ከሚያስብ ሰው ጋር ያለ ወዳጅነት የሰውን የሰማያዊ አስተሳብ ያጠፋል፡፡ በቁሳቁስ ላይ ብቻ ከሚያተኩር  ሰው ጋር ያለ ባልንጀርነት ስለመንፈሳዊ ያለን ትኩረት ቢያደበዝዘው አያስገርምም፡፡ ስለሆድ ብቻ ከሚያስብ ሰው ጋር ያለ ባልንጀርነት  ይዋል ይደር እንጂ የፍቅርና የአገልግሎት ዘርን ከውስጣችን ያመክነዋል፡፡ ስለጥርጥር ከሚያስብ ሰው ጋር ያለ ግንኙነት እምነታችንን ባይጎዳው ይገርማል፡፡    
መልካሙን አመል ከመጠበቅ ይልቅ ከክፉ ባልንጀርነት ራስህን መጠበቅ ይቀላል፡፡ በክፉ ባልንጀርነት መካካል መልካምን አመል ለመጠበቅ ከመሞከር ይልቅ ክፉ ባልንጀርነት ላይ መጨከንና ከክፉ ባልንጀርነት ፈጥኖ መለየት ይቀላል፡፡ በክፉ ባልንጀርነት ውስጥ መልካም አመልይ ይዞ ከመቆየት ይልቅ ክፉ ባልንጀርነትን በፍጥነት መቁረጥ በቀላሉ ከመከራ ይገላግላል፡፡
አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15፡33
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ወዳጅ #ጓደኛ #መታመን #ጥበብ #ፍቅር #ባልንጀርነት #መልካም #አመል #ክፉ #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ጌታ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #እምነት #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ምህረት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment