Popular Posts

Tuesday, March 28, 2017

የሁለቱ ቅርጫቶች ባለቤት ታሪክ

አንድ የሰማሁትን ልብ የሚነካ ታሪክ ላካፍላችሁ፡፡ ታሪኩ በጣም ልቤን ስለነካኝና ስላስደነገጠኝ ምን ያህል ጊዜ ለሰዎች እንደተናገርኩት አላስታውሰውም፡፡
ታሪኩ እንደዚህ ነው፡፡ አንድ ክርስትያን ስለ አንዲት ክርስቲያን ሲፀልይ ራእይ ያያል፡፡ በራእዩም ውስጥ ሁለት ቅርጫቶችን ይመለከታል፡፡ አንደኛው ቅርጫት ሙሉ ነው ፡፡ አንደኛው ቅርጫት ግን ከሞላ ጎደል ባዶ ነው ማለት ይቻላል፡፡ ይህ ክርስትያን ይህ ምንድነው ብሎ ጌታን ሲጠይቅ እግዚአብሄር ተናገረው፡፡
ይህ የምታየው የሞላው ቅርጫት የዚህች ሴት ልመናዋ ነው፡፡ ይህች ሴት መለመን ታውቅበታለች፡፡ ስለዚህ በትጋት ትለምነኛለች፡፡ ይህ የምታየው ከሞላ ጎደል ባዶው የዚህች ሴት የምስጋና ህይወትዋ ነው፡፡ ይህች ሴት እኔን እንዴት እንድምታመሰግን አታውቅም፡፡ እኔን ለማመስገን አትተጋም፡፡ እኔ ደግሞ ልመናዋን መመለስ እፈልጋለሁ፡፡
ለዚህች ሴት እንዲህ ብለህ ነገራት፡፡ እኔን ማመሰገን ጀምሪ፡፡ እኔን በነገር ሁሉ ማመስገን ተማሪ፡፡ እኔን የሚያመሰግን ህይወት ይኑርሽ፡፡ እኔን በትጋት ማመስገን ስትጀምሪ ይህ የፀሎት ልመናሽ ሁሉ እየተመለሰ ይሄዳል ብሎ ተናገረው፡፡
ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ። 1 ጢሞቴዎስ 2፡2
በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ። ፊልጵስዩስ 4፡6
ወደ ደጆቹ በመገዛት፥ ወደ አደባባዮቹም በምስጋና ግቡ፤ አመስግኑት፥ ስሙንም ባርኩ፤ መዝሙር 100፡4
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ማካፈል share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #አመስግኑ #መልካም #እምነት #ቃልኪዳን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #የዘላለምህይወት #ቸር #መንፈስ #መንፈስቅዱስ

No comments:

Post a Comment