Popular Posts

Sunday, December 15, 2019

ዕውር ነውና፥ በቅርብም ያለውን ብቻ ያያል



እነዚህ ነገሮች የሌሉት ዕውር ነውና፥ በቅርብም ያለውን ብቻ ያያል፥ የቀደመውንም ኃጢአቱን መንጻት ረስቶአል። 2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 1፡9
የሰው ብስለት እና በእግዚአብሄር መንግስት ጠቃሚነት ደረጃ ከሚለካባቸው መመዘኛዎች አንዱ የእይታ ርቀት ነው፡፡ ሰው እይታው ቅርብ ከሆነ አልተረዳም ህፃን መማር አለበት ማለት ነው፡፡ ሰው እይታው ሩቅ ከሆነ ብስለት አለው በብዙ ይጠቅማል ማለት ይቻላል፡፡
ዛሬ ስለሚበላውና ስለሚጠጣው ብቻ የሚያስብና ለሩቁ ዋጋ የማይሰጥ ሰው ከእግዚአብሄርም ከሰውም ጋር ዘለቄታዊ ወዳጅነት ሊኖረው አይችልም፡፡
እንደ ሰው በኤፌሶን ከአውሬ ጋር ከታገልሁ፥ ሙታንስ የማይነሡ ከሆነ፥ ምን ይጠቅመኛል? ነገ እንሞታለንና እንብላና እንጠጣ። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15፡32
እግዚአብሄር ለታላላቅ ነገር አጭቶን እያለ እይታው ቅርብ ብቻ የሆነ ሰው ምስኪን ነው፡፡
አንተ ታናሽ መንጋ፥ መንግሥትን ሊሰጣችሁ የአባታችሁ በጎ ፈቃድ ነውና አትፍሩ። የሉቃስ ወንጌል 12፡32
ለጊዜያዊ ለቅርቡ ብቻ እግዚአብሄርን ተስፋ የሚያደርግ ሰው ምስኪን ሰው ነው፡፡  
በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15፡19
ሰው እይታው ራቅ ሲል የዛሬ ደስታውን ገድቦ ለነገ ፍሬያማነቱ በትጋት ይሰራል፡፡
የእምነታችንንም ራስና ፈጻሚውን ኢየሱስን ተመልክተን፥ በፊታችን ያለውን ሩጫ በትዕግሥት እንሩጥ፤ እርሱ ነውርን ንቆ በፊቱም ስላለው ደስታ በመስቀል ታግሦ በእግዚአብሔር ዙፋን ቀኝ ተቀምጦአልና። ወደ ዕብራውያን 12፡1-2
ሰው መንገዱ እይታው ሩቅ ሲሆን በህይወቱ ኢንቨስት የሚያደርገው ነገር ብዙ ይሆናል፡፡
ሰው እይታው ራቅ ሲል ጊዜያዊ ደስታን ይንቃል ለዘላቂው ደስታ ዋጋ ይከፍላል፡፡
ከግብፅም ብዙ ገንዘብ ይልቅ ስለ ክርስቶስ መነቀፍ እጅግ የሚበልጥ ባለ ጠግነት እንዲሆን አስቦአልና ለጊዜው በኃጢአት ከሚገኝ ደስታ ይልቅ ከእግዚአብሔር ሕዝብ ጋር መከራ መቀበልን መረጠ፤ ብድራቱን ትኵር ብሎ ተመልክቶአልና። ወደ ዕብራውያን 11፡25-26
ሰው እይታው ቅርብ ሲሆንና ለሩቁ የእግዚአብሄር ሃሳብ ሲታወር በጊዜያዊው ነገር ዘለቄታዊውን ክብር ያጣዋል፡፡  
እናንተ እርስ በርሳችሁ ክብር የምትቀባበሉ ከአንዱም ከእግዚአብሔር ያለውን ክብር የማትፈልጉ፥ እንዴት ልታምኑ ትችላላችሁ? የዮሐንስ ወንጌል 5፡44
እይታው ቅርብ የሆነ ሰው ህይወቱን የሚያባክነው በሚጠፋው መብል ላይ ነው፡፡  
ለሚጠፋ መብል አትሥሩ፤ ነገር ግን ለዘላለም ሕይወት ለሚኖር መብል የሰው ልጅ ለሚሰጣችሁ ሥሩ፤ እርሱን እግዚአብሔር አብ አትሞታልና። የዮሐንስ ወንጌል 527
እይታው ሩቅ የሆነ ሰው የሚተጋው ስለእምነት ስራ በአይን ስለማይታየው ነገር ነው፡፡
እንግዲህ፦ የእግዚአብሔርን ሥራ እንድንሠራ ምን እናድርግ? አሉት። ኢየሱስ መልሶ፦ ይህ የእግዚአብሔር ሥራ እርሱ በላከው እንድታምኑ ነው አላቸው። የዮሐንስ ወንጌል 5፡28፣29
እይታው ሩቅ የሆነ ሰው
መጨረሻቸው ጥፋት ነው፥ ሆዳቸው አምላካቸው ነው፥ ክብራቸው በነውራቸው ነው፥ አሳባቸው ምድራዊ ነው። እኛ አገራችን በሰማይ ነውና፥ ከዚያም ደግሞ የሚመጣ መድኃኒትን እርሱንም ጌታን ኢየሱስ ክርስቶስን እንጠባበቃለን፤ ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 3፡19፣20
እንግዲህ ከክርስቶስ ጋር ከተነሣችሁ፥ ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ እሹ፤ በላይ ያለውን አስቡ እንጂ በምድር ያለውን አይደለም። ወደ ቆላስይስ ሰዎች 3፡1-2
እይታው ቅርብ ያልሆነ ሰው በምድር ላይ በትጋት የሚሰራው እና የምድሩን መከራ የሚታገሰው ለዘላማዊው ሽልማት ነው፡፡
እነሆ፥ ቶሎ ብዬ እመጣለሁ፤ ማንም አክሊልህን እንዳይወስድብህ ያለህን አጽንተህ ያዝ። የዮሐንስ ራእይ 3፡11
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #እይታ #ተስፋ #መፀለይ #መንፈስ #በረከት #መዝገብ #ሰማይ #እንግዶች #ዘላለም #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #እምነት #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እይታ #ምድራዊ #ሰማያዊት #ማየት #ቅርብ

No comments:

Post a Comment