Popular Posts

Tuesday, December 10, 2019

እግዚአብሄር የሚረዳበት ብቸኛው መንገድ



እግዚአብሄር መንገዱ ብዙ ነው፡፡ እግዚአብሄር አሰራሩ ልዩ ልዩ ነው፡፡ እግዚአብሄር ባላሰብነው መንገድ ሲረዳን አይተናል፡፡ እግዚአብሄር ብዙዎችን በተለያ መንገድ ይረዳል፡፡
እግዚአብሄር ቢፈልግም እንኳን በብዙ መንገድ ሊረዳው የማይችለው ሰው አለ፡፡ እግዚአብሄር ቢፈልግ እንኳን በአንድ መንገድ ብቻ ሊረዳው የሚገደድበት ሰው አለ፡፡
የሚማር ልብ የሌለው ሰው የመዳን ተስፋ የሌለው ሰው ነው፡፡
በቃሉ የሚቸኵለውን ሰው ብታይ፥ ከእርሱ ይልቅ ለሰነፍ ተስፋ አለው። መጽሐፈ ምሳሌ 29፡20
ሁሉን አውቃለሁ የሚል ሰው ለመለወጥ ተስፋው የመነመነ ሰው ነው፡፡  
ለራሱ ጠቢብ የሆነ የሚምስለውን ሰው አየኸውን? ከእርሱ ይልቅ ለሰነፍ ተስፋ አለው። መጽሐፈ ምሳሌ 26፡12
እግዚአብሄር በአንድ መንገድ ብቻ ሊረዳው የሚችል ሰው ደግሞ አለ፡፡
እግዚአብሄር ሰውን የሚረዳበት በጣም ብዙ መንገድ ቢኖውርም ትእቢተኛን ግን ሊረዳው የሚችለው በአንድ መንገድ ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን የሚገናኝበት ብዙ መንገድ ቢኖረውም ከትእቢተኛ ጋር በአንድ መንገድ ብቻ እንዲገናኝ ይገደዳል፡፡
እግዚአብሄር ትእቢተኛውን የሚገናኘው በተቃራኒው ጎን ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሄር ትእቢተኛውን የሚገናኘው ትእቢተኛውን ፊትለፊት በመግጠም ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሄር ትእቢተኛውን የሚገናኘ ትእቢተኛውን በማሳየት ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሄር ትእቢተኛውን የሚገናኘው በመጋፈጥ ብቻ ነው፡፡ እግዚአብሄር ትእቢተኛውን  የሚገናኘው በተቃውሞ ብቻ ነው፡፡
ሰው የተፈጠረው በእግዚአብሄር መልክና አምሳል ነፃ ፈቃድ ያለው ተደርጎ ነው፡፡ ሰው ትእቢትን ከመረጠ ማንም ከምርጫው ሊመልሰው አይችልም፡፡ የፈጠረን እግዚአብሄር እንኳን በእኛ ፋንታ አይመርጥልንም፡፡ እግዚአብሄር እንኳን ሊያደርግ የሚችለው የትህትናና የትእቢትን ምርጫዎች መስጠትና ትህትናን እንዲመርጥ  መምከር ብቻ ነው፡፡
በፊታችሁ ሕይወትንና ሞትን በረከትንና መርገምን እንዳስቀመጥሁ እኔ ዛሬ ሰማይንና ምድርን በአንተ ላይ አስመሰክራለሁ፤ እንግዲህ አንተና ዘርህ በሕይወት ትኖሩ ዘንድ ሕይወትን ምረጥ፤ ኦሪት ዘዳግም 30፡19
እግዚአብሄር ለትሁታን ፀጋ ቢሰጥም ለትእቢተኛው ግን ከተቃውሞ ውጭ ምንም ሊሰጠው አይችልም፡፡  
ነገር ግን ጸጋን አብልጦ ይሰጣል፤ ስለዚህ፦ እግዚአብሔር ትዕቢተኞችን ይቃወማል፥ ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል ይላል። የያዕቆብ መልእክት 4፡6
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ትህትና #መዋረድ #ባህሪ #ዝቅታ #ትዕቢት #ትምክህት #መመካት #ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ጥፋት #ውድቀት #ኩሩ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment