Popular Posts

Tuesday, July 9, 2019

ፍቅር አይወድቅም



ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም፤ ትንቢት ቢሆን ግን ይሻራል፤ ልሳኖች ቢሆኑ ይቀራሉ፤ እውቀትም ቢሆን ይሻራል። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 13፡8
ፍቅር ዘላለማዊ ነው፡፡
ፍቅር የእግዚአብሄር ባህሪ ነው፡፡ እግዚአብሄር ፍቅር ነው፡፡ እግዚአብሄር እንደማይወድቅ ሁሉ ከእግዚአብሄር የሚገኘውና በእግዚአብሄር የሚደገፈው ፍቅር አይወድቅም፡፡ እግዚአብሄር ዘላለማዊ እንደሆነ ሁሉ ፍቅር ዘላለማዊ ነው፡፡ እግዚአብሄር ጊዜው እንደማያልፍበት ሁሉ ፍቅር ጊዜው አያልፍበትም፡፡ እግዚአብሄር ጊዜ እንደማይሽረው ሁሉ ፍቅር ጊዜ አይሽረውም፡፡
ወዳጆች ሆይ፥ ፍቅር ከእግዚአብሔር ስለ ሆነ፥ የሚወደውም ሁሉ ከእግዚአብሔር ስለ ተወለደ እግዚአብሔርንም ስለሚያውቅ፥ እርስ በርሳችን እንዋደድ። ፍቅር የሌለው እግዚአብሔርን አያውቅም፥ እግዚአብሔር ፍቅር ነውና። 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4፡7-8
ፍቅር ጊዜያዊ አይደለም፡፡
ፍቅር የአንድ ሰሞን አይደለም፡፡ ፍቅር ወረት አያውቅም፡፡ ፍቅር አይለወጥም፡፡
ፍቅር ሃያል ነው፡፡
ፍቅር የሚያሸንፈው የለም፡፡ ፍቅር ምንም ህግ አይገዛውም፡፡ ፍቅርንብ የሚከለክል ህግ የለም፡፡ ፍቅርን የሚረታ ስልጣን የለም፡፡
የመንፈስ ፍሬ ግን ፍቅር፥ ደስታ፥ ሰላም፥ ትዕግሥት፥ ቸርነት፥ በጎነት፥ እምነት፥ የውሃት፥ ራስን መግዛት ነው። እንደዚህ ያሉትን የሚከለክል ሕግ የለም። ወደ ገላትያ ሰዎች 5፡22-23
ፍቅር ደካማ አይደለም፡፡
ፍቅር በሁኔታዎች የሚደገፍ ደካማ አይደልም፡፡ ፍቅር አሸናፊ ነው፡፡ ፍቅር ሁሉን ይረታል፡፡ ፍቅር እንደሁኔተው ይሚለዋወጥ አይደለም፡፡ ፍቅር የራሱ የማይለወጥ መርህ ያለው ባህሪ ነው፡፡
ፍቅር ቋሚ እና ዘላቂ ነው፡፡
ፍቅር ዘላቂ ነው፡፡ ፍቅር አይለወጥም፡፡ ፍቅር አይቆምም፡፡
ፍቅር ጊዜያዊ አይደለም፡፡
ፍቅር የውሳኔ ጉዳይ ነው፡፡ ፍቅር የመረዳት ነገር ነው፡፡ ፍቅር ስሜታዊ አይደለም፡፡ ፍቅር ዛሬ ታይቶ ነገ የሚጠፋ አይደለም፡፡ ፍቅር እስከ መጨረሻው ይሄዳል፡፡
ፍቅር ያሸንፋል፡፡ በብዙ ነገር የማይረቱ አሉ፡፡ ፍቅር የማይረታው ሰው ግን ማንም የለም፡፡ የየሰው መረዳት እንደሰው አይነት ይለያያል፡፡ ብዙ ነገርን ሊረዳ የማይችል ብዙ ሰው አለ፡፡ ፍቅርን ሊረዳ የማይችል ሰው ግን የለም፡፡ ብዙ ነገር የማይማረከው ሰው አለ፡፡ ፍቅር የማይማረከው ሰው ግን የለም፡፡
እርስ በርሳችሁ ፍቅር ቢኖራችሁ፥ ደቀ መዛሙርቴ እንደ ሆናችሁ ሰዎች ሁሉ በዚህ ያውቃሉ። የዮሐንስ ወንጌል 13፡35
ፍቅር ለዘወትር አይወድቅም፤ 1 ቆሮንቶስ 138
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ፍቅር #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #ቸርነት #ትግስት #ፍርሃት #መታበይ #መመካት #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment