Popular Posts

Friday, July 19, 2019

የሰው መጠቀሚያ የመሆን ስሜት



እውነትም እያንዳንዳችን አንዳንዴ ሌላው ሰው ካላግባብ እንደተጠቀመብን ይሰማናል::
ከሰው ጋር እየኖረና እየሰራ ይህ አይነት ስሜት በየጊዜው የማይሰማው ሰው አይገኝም:: አንዳንዴ መሪው ተመሪው እንደተጠቀመበት ይሰማዋል:: ተመሪው  መሪው እንደተጠቀመበት ይሰማዋል:: አንዳንዴ ፓስተሩ ምእመኑ እንደተጠቀመበት ይሰማዋል:: ምእመኑ ፓስተሩ እንደተጠቀመበት ይሰማዋል:: አንዳንዴ አሰሪው ሰራትኛው እንደተጠቀመበት ይሰማዋል:: ሰራተኛው አሰሪው እንደተጠቀመበት ይሰማዋል::
አንዳንዴ እጅግ ቅርብ በሆኑት በባልና በሚስት ላይ እንኳን እንደዚህ አይነት ሌላው ተጠቀመበኝ ስሜት ይንፀባረቃል:: አንዳንዴ ሚስት ባልዋ እንደተጠቀመባት ይሰማታል:: ባል ሚስቱ እንደተጠቀምችበት ይሰማዋል::
እንዳንዴ ሌላው ተጠቀምብኝ የሚለውን ሁሉ ስንሰማ ይህ ሁሉ ጥቅም የት ገባ ብለን እንጠይቃለን::
እውነት ነው ድንበራችንን ካላወቅንና ካላሳወቅ ድንበራቸውን የማያውቁ እና ካላግባብ ሊጠቀሙብን የሚፈልጉ ሰዎች ይኖራሉ:: ነገር ግን ሌላው ሰው ተጠቀመብን የሚለውን ስሜታችንን ሁሉ ካመንነው ደግሞ ሰላማችንን እናጣለን::
ሌላው ተጠቀመብን የሚለው ስሜት ሁሌም ባይሆንም አንዳንዴ ከራስ ወዳድነትና ከስስት ይመጣል፡፡ እኛ ይበልጥ እንደለፋን ስናስብ መነጫነጭ እንጀምራለን፡፡ በማንኛውም አጋርነት አንተ ሃምሳ በመቶ እኔ ሃምሳ በመቶ እናዋጣለን ተብሎ የሚሰመርበት ሁኔታ የለም፡፡ በቃል ደረጃ እንለዋለን እንጂ አንዱ አንዳንድ ጊዜ ሰባ በመቶ የሚያዋጣበት ለዔላው ሃምሳ በመቶ የሚያዋጣበት ሁኔተ ይፈጠራል፡፡ በሌላ ጊዜ ድግሞ ሰላሳ በመቶ ያዋጣው ስልሳ በመቶ የሚያዋጣበትና ሌላው አርበና በመቲ የሚያዋጣበት ሁኔታ ደግሞ ይፈጠራል፡፡
የሰው ብድራት ያለው በእግዚአብሄር ዘንድ እንደሆነ የሚያምን ሰው ብዙ በማዋጣቱ እንደተጠቀመ ደስ እያለው ይሄዳል እንጂ አይነጫነጭም፡፡
ባሪያ ቢሆን ወይም ጨዋ ሰው፥ እያንዳንዱ የሚያደርገውን መልካም ነገር ሁሉ ከጌታ በብድራት እንዲቀበለው ታውቃላችሁና። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 6፡8
ሰዎች ቢጠቀሙብን ብንበደል እንኳን የሚክሰን እግዚአብሄር አለ፡፡ ከመበደል መበደል ይሻላል፡፡
እንግዲህ ፈጽሞ የእርስ በርስ ሙግት እንዳለባችሁ በእናንተ ጉድለት ነው። ብትበደሉ አይሻልምን? ብትታለሉስ አይሻልምን? 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6፡7
የሚያፅናናን ነገር ግን ሰው ሊጠቀምብን የሚፈልገው ጠቃሚ ስለሆንን ነው:: ከሌላ ሰው ጥቅም ያልፈለገው ሰው ከእኛ ጥቅም ቢፈልግ ሰውን መጥቀም መቻላችን በራሱ ክብራችን ነው፡፡
እንዲሁ እናንተ ደግሞ የታዘዛችሁትን ሁሉ ባደረጋችሁ ጊዜ፡የማንጠቅም ባሪያዎች ነን፥ ልናደርገው የሚገባንን አድርገናል፡ በሉ። የሉቃስ ወንጌል 17:10
ሰው ሊጠቀምብን የሚፈልገውም እንዳንጠቀምበት ፈርቶ ከስጋት ከመነጨ ስሜት ሊሆን ይችላል:: እንዳልተጠቀምንበት ስጋቱን የምንቀንሰው ገፋ አድርገን እንዲጠቀምብን ስንፈቅድለት ነው::
ማንም ሰው አንድ ምዕራፍ ትሄድ ዘንድ ቢያስገድድህ ሁለተኛውን ከእርሱ ጋር ሂድ። የማቴዎስ ወንጌል 5፡41
እግዚአብሄር በሰጠን ፀጋ ከሌላው ሰው እንደተሻልን የምናሳየውና በእግዚአብሄር የሚያስችል ሃይል የምንኩራራው ተጨማሪውን ምእራፍ በራሳችን ፈቃድ ስንሄድ ነው፡፡
የሆነ ሆኖ ተጠቀምክበትና ተጠቀመብህ የሚለው ጥያቄና ስሜት ቀላል መልስ ያለው  ጥያቄ አይደለም:: ሰውን እናንተ እንዳልተጠቀማችሁበት ወይም ሌላው እንደተጠቀመባቹ በንግግር ከማሳመን ይልቅ ክርክር ያስነሳውን ጥቅማችሁ የተባለውን ነገር መተው ይቀላል::
መፍቀድ የሌለባችሁ ግልፅ የሆነ አላግባበ መጠቀም ካልሆነ በስተቀር አግባብና አላግባብ የሆነውን መጠቀም ለመለየት ቀላል አይደለም፡፡ ስለዚህ ሰውን እናንተ እንዳልተጠቀማችሁበት ወይም ሌላው እንዳልተጠቀምባቹ በንግግር ከማሳመን ይልቅ ክርክር ያስነሳውን ጥቅማችሁ የተባለውን ነገር መተው ውጥረት ይቀንሳል ሰላምን ይሰጣል::
ቢቻላችሁስ በእናንተ በኩል ከሰው ሁሉ ጋር በሰላም ኑሩ። ወደ ሮሜ 12:18
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa37/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪ #ፀጋ #የሚያስችልሃይል #እውቀት #ምስጋና #ትህትና #ልብ #እምነት #ፀሎት #ማማጠን #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ትጋት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment