Popular Posts

Friday, July 5, 2019

ይህም በእግዚአብሔር ዓይን ቀላል ነገር ነው


እንዲህም አለ፦ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በዚህ ሸለቆ ሁሉ ጕድጓድ ቆፈሩ። እግዚአብሔርም እንዲህ ይላል፦ ነፋስ አታዩም፥ ዝናብም አታዩም፥ ይህ ሸለቆ ግን ውኃ ይሞላል፤ እናንተም ከብቶቻችሁም እንስሶቻችሁም ትጠጣላችሁ። ይህም በእግዚአብሔር ዓይን ቀላል ነገር ነው፤ ደግሞም ሞዓባውያንን በእጃችሁ አሳልፎ ይሰጣል። መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ 3:16-18
ይህም በእግዚአብሔር ዓይን ቀላል ነገር ነው፡፡
ብዙ ጊዜ የእግዚአብሄርን ክንድ አይተናል ነገር ግን አሁን ስላለንበት ሁኔታ ደግሞ ይህንንም ሊያደርግ ይችላል ብለን እናስባለን፡፡ መልሱ ግን ያ አላልፍም ብለህ ግን ያለፍክበት ሁኔታ ብቻ ሳይሆን ይህም በእግዚአብሔር ዓይን ቀላል ነገር ነው፡፡ ያንን አለልፍም ብለህ ያለፍክበት ሁኔታን እንደለወጠ ሁሉ ይህንንም ሊለውጥ ይችላል፡፡ ለሰው የማይቻል ለእግዚአብሄር ይቻላል፡፡  
እርሱ ግን፦ በሰው ዘንድ የማይቻል በእግዚአብሔር ዘንድ ይቻላል አለ። የሉቃስ ወንጌል 18፡27
ብዙ ጊዜ ተስፋ እንድንቆርጥና ወደኋላ እንድንመለስ የሚፈትነንም በአካባቢያችን ስለሁኔታው እውነተኝነት የሚመሰክሩ ምልክቶች አለመኖራቸው ነው፡፡
እግዚአብሄር ለዚህም መልስ አለው፡፡ በትክክለኛው መንገድ ላይ መሆናችሁ ምልክቱ ስለሁኔታው እውነተኝነት የሚመሰክሩ ምልክቶች አለማየታችሁ ነው፡፡
እግዚአብሔርም እንዲህ ይላል፦ ነፋስ አታዩም፥ ዝናብም አታዩም፥ ይህ ሸለቆ ግን ውኃ ይሞላል፡፡
የፈራችሁትም ውድቀት አይደርስባችሁም፡፡
እናንተም ከብቶቻችሁም እንስሶቻችሁም ትጠጣላችሁ።
ውድቀት አይደርስባችሁም ብቻ ሳይሆን በህይወታችሁ እውነተኛውን ድል ታገኛላችሁ፡፡ በዚህም እግዚአብሄር የልባችሁ መሻት ይሞላል፡፡
ደግሞም ሞዓባውያንን በእጃችሁ አሳልፎ ይሰጣል።
ምክንያቱም ይህም በእግዚአብሔር ዓይን ቀላል ነገር ነው፡፡
እግዚአብሄርን የሚያሳስበው ሰውን የሚያሳስበ አይደለም፡፡ ሰውን የሚያሳስብው ውሃ አለመምጣቱ ነው፡፡ እግዚአብሄርን የሚያሳስበው ነገር በእግዚአብሄር አይን ቀላል የሆነውን ነገር እግዚአብሄር ሲያደርግ ሰው ለታእምሩ አለመዘጋጀቱ ነው፡፡ የሰው ትኩረት ታእምሩ እንዴት እንደሚሆን ነው፡፡ የእግዚአብሄር ትኩረት ሰው ተአምሩን እንዴት በሚገባ እንደሚጠቀምበት ነው፡፡
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በዚህ ሸለቆ ሁሉ ጕድጓድ ቆፈሩ።
እንዲህም አለ፦ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ በዚህ ሸለቆ ሁሉ ጕድጓድ ቆፈሩ። እግዚአብሔርም እንዲህ ይላል፦ ነፋስ አታዩም፥ ዝናብም አታዩም፥ ይህ ሸለቆ ግን ውኃ ይሞላል፤ እናንተም ከብቶቻችሁም እንስሶቻችሁም ትጠጣላችሁ። ይህም በእግዚአብሔር ዓይን ቀላል ነገር ነው፤ ደግሞም ሞዓባውያንን በእጃችሁ አሳልፎ ይሰጣል። መጽሐፈ ነገሥት ካልዕ 3:16-18
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
 ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
 #ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #መናገር #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ቃል #ማሰላሰል #ማድረግ #ሁሉይቻላል #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment