Popular Posts

Friday, July 19, 2019

መታዘዝ እንጂ መሥዋዕት እግዚአብሄርን ደስ አያሰኘውም



መሥዋዕትን ብትወድድስ በሰጠሁህ ነበር የሚቃጠለውም መሥዋዕት ደስ አያሰኝህም። የእግዚአብሔር መሥዋዕት የተሰበረ መንፈስ ነው፥ የተሰበርውንና የተዋረደውን ልብ እግዚአብሔር አይንቅም። መዝሙረ ዳዊት 51፡16-17
እውነተኛ አምልኮት በራስ ግምት እግዚአብሄርን ለማምለክ ከመሞከር ተስፋ መቁረጥ ነው፡፡ እውነተኛ አምልኮት በራስ መስዋእት ተስፋ ከመቁረጥ ይጀመራል፡፡ እውነተኛ አምልኮ መስዋእትን ማቅረብ ሳይሆን እግዚአብሄር የጠየቀንን ነገር ለመታዘዝ መስዋእት መሆን ነው፡፡
መሥዋዕትንና ቍርባንን አልወደድህም፤ ሥጋን አዘጋጀህልኝ፤ የሚቃጠለውንና ስለ ኃጢአት የሚቀርበውን መሥዋዕት አልሻህም። በዚያን ጊዜ አልሁ፦ እነሆ፥ መጣሁ፤ ስለ እኔ በመጽሐፍ ራስ ተጽፎአል፤ አምላኬ ሆይ፥ ፈቃድህን ለማድረግ ወደድሁ፥ ሕግህም በልቤ ውስጥ ነው። መዝሙረ ዳዊት 40፡6-8
እውነተኛ አምልኮ እግዚአብሄር ይህን ባቀርብለት መልካም ነው በማለት መስዋእትን ማቅረብ ሳይሆን እግዚአብሄር እንድናደርግ ያዘዘንን ያንን ብቻ መታዘዝ ነው፡፡ እውነተኛ አምልኮ የእግዚአብሄር ፈቃድ መሆኑን በልባችን የሰማነውን ነገር ማድረግ ነው፡፡
ሳሙኤልም፦ በውኑ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ደስ እንደሚለው እግዚአብሔር በሚቃጠልና በሚታረድ መሥዋዕት ደስ ይለዋልን? እነሆ፥ መታዘዝ ከመሥዋዕት፥ ማዳመጥም የአውራ በግ ስብ ከማቅረብ ይበልጣል። መጽሐፈ ሳሙኤል ቀዳማዊ 15፡22
የአምልኮት መልክ ብቻ ያለው ሰው እግዚአብሄርን አያውቅም አይከተልም፡፡ የአምልኮት መልክ ብቻ ያለው ሰው ምህረትን አያውቅም አይከተልም፡፡ የአምልኮት መልክ ያለው ሰው እግዚአብሄርን መታዘዝን በራስ ግምት እግዚአብሄርን በስጦታ ለማስደሰት በመሞከር ይለውጠዋል፡፡ የአምልኮት መልክ የእውነተኛ መንፈሳዊነት ማስመሰያ ፌክ ነው፡፡
የአምልኮት መልክ አላቸው ኃይሉን ግን ክደዋል፤ ከእነዚህ ደግሞ ራቅ። 2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 3፡5
የአምልኮት መልክ ብቻ ያለው ሰው የሃይማኖት ወጎችንና ስርአቶችን አይፈፅምም ማለት አይደለም፡፡ የአምልኮት መልክ ብቻ ያለው ሰው እንደ ማንኛውም አምላኪ የሃይማኖት ወጎችንና ስርአቶችን ይፈፅማል፡፡ የአምልኮት መልክ ብቻ ያለው ሰው በራሱ ግምት እግዚአብሄር ይሄን ሊፈልግ ይችላል እያለ በግምት መስዋእትን ያቀርባል፡፡ የአምልኮት መልክ ብቻ ያለው ሰው የእግዚአብሄርን ትእዛዝ ከማድረግ ውጭ ሃይማኖታዊ ወጎችንና ስርአቶችን ሁሉ ይፈፅማል፡፡
ከመሥዋዕት ይልቅ ምሕረትን፥ ከሚቃጠልም መሥዋዕት ይልቅ እግዚአብሔርን ማወቅ እወድዳለሁና። ትንቢተ ሆሴዕ 6፡6
የአምልኮት መልክ ብቻ ያለው ሰው መንገዱ በፊቱ የቀናች ትመስለዋለች፡፡ የአምልኮት መልክ ብቻ ያለው ሰው እግዚአብሄርን እያገለገለ ይመስለዋል፡፡ የአምልኮት መልክ ብቻ ያለው ሰው ስርአትና ወግ ስለፈፀመ ብቻ እግዚአብሄርን የሚያስደስት ይመስለዋል፡፡
እግዚአብሄር ግን ሰው እግዚአብሄርን አስደስትበታለሁ ብሎ  በሚገምተው የግምት መስዋእት አይደሰትም፡፡
የሰው መንገድ ሁሉ በዓይኑ ፊት የቀናች ትመስለዋለች፤ እግዚአብሔር ግን ልብን ይመዝናል። እግዚአብሔር ከመሥዋዕት ይልቅ ጽድቅንና ቅን ነገርን ማድረግ ይወድዳል። መጽሐፈ ምሳሌ 21፡2-3
እግዚአብሄር የሚፈልገውን ያውቃል፡፡ እግዚአብሄር ከሰው የሚፈልገው ከእግዚአብሄር ጋር መቆምን እግዚአብሄርን በቃሉ መታዘዝን ነው፡፡ እግዚአብሄር እውነተኛ መስዋእት የሚለው እርሱን ሰምቶ መታዘዝን እንጂ መልካም የሚመስልን ነገር ለእግዚአብሄር ማድረግን አይደለም፡፡ ለእግዚአብሄር ከምናደርግለት ብዙ መስዋእት ይልቅ ድምፁን በመታዘዛችን ይደሰታል፡፡
መሥዋዕትንና ቍርባንን አልወደድህም፤ ሥጋን አዘጋጀህልኝ፤ የሚቃጠለውንና ስለ ኃጢአት የሚቀርበውን መሥዋዕት አልሻህም። በዚያን ጊዜ አልሁ፦ እነሆ፥ መጣሁ፤ ስለ እኔ በመጽሐፍ ራስ ተጽፎአል፤ አምላኬ ሆይ፥ ፈቃድህን ለማድረግ ወደድሁ፥ ሕግህም በልቤ ውስጥ ነው። መዝሙረ ዳዊት 40፡6-8
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiydinsa7/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#የእግዚአብሄርምክር #የእግዚአብሔርፈቃድ #እግዚአብሔር #እንደተፃፈ #ማታዘዝ #መባ #መሥዋዕት ##እምነት #የሰውአሳብ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ 

No comments:

Post a Comment