Popular Posts

Sunday, October 2, 2016

የወንድሞች ህብረት

እግዚአብሄር በመልኩና በምሳሌው ስለፈጠረን እግዚአብሄር እንደኛው ስሜት እንዳለው እንረዳለን፡፡ እግዚአብሄርን የሚያስደስቱን ነገሮች አሉ፡፡ እግዚአብሄርን የማያስደንቁት ነገሮች አሉ፡፡ እግዚአብሄር የሚወደው ነገር አለ፡፡ እግዚአብሄር የማይወደው ነገር ደግሞ አለ፡፡ ለእግዚአብሄር መልካም የሆነ ነገር አለ፡፡ እግዚአብሄር መልካም የማይለው ነገር አለ፡፡
እኛን የሚያስደንቁን ነገሮች ነገሮች ሁሉ እግዚአብሄርን አያስደንቁትም፡፡ እግዚአብሄርን የማያስደስቱት እኛን የሚያስደስቱን ነገሮች አሉ፡፡
በመፅሃፍ ቅዱስ እግዚአብሄር የሚደነቅባቸውና መልካም ነው ያማረ ነው ብሎ የሚናገረው ነገር አለ፡፡ እንዲያውም የወንድሞች ህብረት ለእግዚአብሄር የሚጣፍጥ ምርጥ ሽቱ እንደሆነ መፅሃፍ ቅዱስ በግልፅ ይናገራል፡፡ የወንድሞች መሰብሰብ ጥምን እንደሚያረካና እንደሚያለመልም ውሃ ወሳኝ እንደሆነ መፅሃፍ ቅዱስ ያስተምራል፡፡
ስንሰበሰብ እግዚአብሄር ደስ ይለዋል፡፡ በአንድነት ስንሆን ደስ ይረካል፡፡ የወንድሞች መሰብሰብ ለእግዚአበሄር እንደ ሽቱ ነው፡፡ ወንድሞች በኅብረት ቢቀመጡ፥ እነሆ፥ መልካም ነው፥ እነሆም፥ ያማረ ነው።ከራስ እስከ ጢም እንደሚፈስስ፥ እስከ አሮን ጢም፥ በልብሱ መደረቢያ እንደሚወርድ ሽቱ ነው። በጽዮን ተራሮች እንደሚወርድ እንደ አርሞንዔም ጠል ነው፤ በዚያ እግዚአብሔር በረከቱን ሕይወትንም እስከ ዘላለም አዝዞአልና። መዝሙር 133:1-3 ይህንን ፅሁፍ ሼር ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ህብረት #ወንድሞች #ሽቱ #ያማረ #እምነት #አንድነት #ልብ #ቃል #ምስጉን #ሃሳብ #ማሰላሰል #ወንጌል #ደቀመዝሙር #ኢየሱስ #ጌታ #መዳን #አማርኛ #ኢትዮጲያ #አቢይዋቁማ #ፌስቡክ #አዋጅ

No comments:

Post a Comment