Popular Posts

Monday, September 9, 2024

መልካም አዲስ ህይወት

 


ስለ ሃጢያታችን በመስቀል ላይ የሞተውን ኢየሱስን ስንቀበል እግዚአብሄር ይቀበለናል ከሞት ወደ ህይወት እንሸጋግራልን የዘላለም ህይወት እናገኛለን። በልጁ ካላመንን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእኛ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አናይም።
በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም። የዮሐንስ ወንጌል 3፥36
ክርስቶስን ካልተቀበልን ልጁ ኢየሱስ በሕይወታችን ስለሌለ ከእግዚአብሄር ርቀን ከእግዚአብሄር ህይወት እንጠፋልን። አዲሱን አመት አዲስ የሚያደርገው በክርስቶስ የተቀበልነው አዲስ ህይወት እንጂ ያው የተለመደው የወር መለዋወጥ አይደለም።
እግዚአብሔርም የዘላለምን ሕይወት እንደ ሰጠን ይህም ሕይወት በልጁ እንዳለ ምስክሩ ይህ ነው። ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም። 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 5፥11-12
እንዲያው በነጻ የተሰጠንን የዘላለም ህይወት ስጦታ በልጁ በኢየሱስ ስንቀበል ብቻ በልጁ አዲስ ህይወትን እንቀበላለን።
መልካም አዲስ አመት
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ  Abiy Wakuma Dinsa
 #ሀበሻ #ዝግ #እግዚአብሔርንመምሰል #ኢየሱስ #ጌታ #ምልጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ምስጋና #እምነት #አበሻ #አማርኛ #ሰላም #ደስታ #አዲስአመት #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ኢትዮጲያ #ፀሎት 


No comments:

Post a Comment