Popular Posts

Saturday, September 28, 2024

ሶስቱ የማይመለሱ ፀሎቶች

 

ሶስቱ የማይመለሱ ፀሎቶች

  1. በስጋ የሚፀለዪ ፀሎቶች 

ፀሎት ክእግዚአብሄር ከአባታችን የምንቀበልበት መንገድ  ቢሆንም የሚያስፈልገንን እንጂ የራስወዳድነታችንን እና የስግብግብነታችንን ፍላጎት የምናስፈፅምበት መድረክ አይደለም:: መሰረታዊፍላጎታችንን እንጂ ቅንጦታችንን የምናሟላበት መሳሪያ አይደለም::              

በእናንተ ዘንድ ጦርና ጠብ ከወዴት ይመጣሉበብልቶቻችሁ ውስጥ ከሚዋጉ ከእነዚህከምቾቶቻችሁ አይደሉምን? 2 ትመኛላችሁ ለእናንተም አይሆንም፤ ትገድላላችሁ በብርቱምትፈልጋላችሁ፥ ልታገኙም አትችሉም፤ ትጣላላችሁ ትዋጉማላችሁ ነገር ግን አትለምኑምና ለእናንተአይሆንም፤ 3 ትለምናላችሁ፥ በምቾቶቻችሁም ትከፍሉ ዘንድ በክፉ ትለምናላችሁና አትቀበሉም።የያዕቆብ መልእክት 4:1-3

2. በስንፍና የሚፀለዪ ፀሎቶች 

ፀሎት የእግዚአብሔርን ፈቃድ ከቃሉ ፈልገን እንደ እግዚአብሔር ቃል በመፀለይ የምንቀበለው እንጂበስንፍና እጃችን ላይ የሚወድቅ እድል አይደለም::            

14 በእርሱ ዘንድ ያለን ድፍረት ይህ ነው፤ እንደ ፈቃዱ አንዳች ብንለምን ይሰማናል። 1 የዮሐንስመልእክት 5:14

3. በጥላቻ ይቅር ባለማለት የሚፀለዪ ፀሎቶች

ፀሎት የእኛን ጥላቻ ማስፈፀሚያ መሳሪያ አይደለም:: ፀሎት በፍቅር የመባረኪያ እንጂእግዚአብሔርን የእኛ ወገን አድርገን የማንቀበለውን ሰው መርገሚያ መሳሪያ አይደለም::

25 ለጸሎትም በቆማችሁ ጊዜ፥ በሰማያት ያለው አባታችሁ ደግሞ ኃጢአታችሁን ይቅር እንዲላችሁ፥በማንም ላይ አንዳች ቢኖርባችሁ ይቅር በሉት።

26 እናንተ ግን ይቅር ባትሉ በሰማያት ያለው አባታችሁም ኃጢአታችሁን ይቅር አይላችሁም።የማርቆስ ወንጌል 11:25-26


አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa


#ፀሎት #ፈቃዱ #መልስ #ኢየሱስ #ጌታ #ጋብቻ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ሚስት #መዳን#መፅሃፍቅዱስ #ባል #እምነት #ወንድ #ፍቅር #ትዳር #ሰላም #ሴት #አቢይ #አቢይዋቁማ#አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ


No comments:

Post a Comment