Popular Posts

Tuesday, January 12, 2021

አቢይ የጥሞና ቃል #ስድስት የእግዚአብሔር መንግሥት ሰላም

 

አቢይ የጥሞና ቃል #ስድስት የእግዚአብሔር መንግሥት ሰላም

የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂ መብልና መጠጥ አይደለችምና። ወደ ሮሜ ሰዎች 14፡17

እግዚአብሄር ንጉስዋ የሆነላትና በመንፈስ በምድር ላይ የምትገዛው የእግዚአብሄር መንግስት ሁለንተናዋ ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ነው፡፡  

ከጽድቅና ከሰላም በመንፈስ ቅዱስም ከሆነ ደስታ አንፃር ውጭ የእግዚአብሄር መንግስት   ልትታይም ሆነ ልትለካ አትችልም፡፡

የእግዚአብሄር መንግስት ሃላፊነትዋም ጥቅምዋም ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ብቻ ነው፡፡

የእግዚአብሄር መንግስት ዜጎችዋን የምትባርክው በፅድቅ እና በሰላም ነው፡፡ የእግዚአብሄር መንግስት ረብሻ በሞላበት አለም ለዜጎችዋ ልዩ የሆነ አእምሮን የሚያልፍ ሰላምን በመስጠት ትታወቃለች፡፡

በእኔ ሳላችሁ ሰላም እንዲሆንላችሁ ይህን ተናግሬአችኋለሁ። በዓለም ሳላችሁ መከራ አለባችሁ፤ ነገር ግን አይዞአችሁ፤ እኔ ዓለምን አሸንፌዋለሁ። የዮሐንስ ወንጌል 16፡33

አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል። ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 4፡7

በእግዚአብሄር መንግስት ውስጥ የሚኖር ሰው ብዙ የሚታይ ነገር ላይኖረው ይችላል ነገር ግን ሰላም የእርሱ ነው፡፡ ለእግዚአብሄር መንግስት የሚገዛ ሰው በመከራ ሊያልፍ ይችላል ነገር ግን ሁለንተናውን አእምሮ የሚያልፍ ሰላም ግን ይቆጣጠረዋል፡፡

የእግዚአብሄር መንግስት ሰዎች በመጀመሪያ ከፈጠራቸው ከእግዚአብሄር ጋር ጥለኛ አይደሉም በክርስቶስ ኢየሱስ መስቀል ታርቀዋል ሰላም ናቸው፡፡

ነገር ግን የሆነው ሁሉ፥ በክርስቶስ ከራሱ ጋር ካስታረቀን የማስታረቅም አገልግሎት ከሰጠን፥ ከእግዚአብሔር ነው፤ እግዚአብሔር በክርስቶስ ሆኖ ዓለሙን ከራሱ ጋር ያስታርቅ ነበርና፥ በደላቸውን 

No comments:

Post a Comment