Popular Posts

Saturday, September 23, 2017

የእውቀት ማጣት አምስቱ ምልክቶች

እውቀት ብርሃን ነው፡፡ ሰው የእግዚአብሄር ቃል እውቀት ከሌላው ነገር ሁሉ ይጨላልምበታል፡፡ ሰው ትክክለኛው የመፀሃፍ ቅዱስ እውቀት ከሌላው ኑሮው በሙከራና በውድቀት የተሞላ ይሆናል፡፡
ሰው በእግዚአብሄር ቃል እውቀት ሲሞላ የእግዚአብሄርን መንግስት በደስታ ማገልገል ይችላል፡፡ ሰው በእግዚአብሄር ቃል እውቀት ሲሞላ ነገሮችን እንደ አመጣጣቸው መያዝ እና ማስተናገድ ይችላል፡፡ ሰው በእግዚአብሄር እውቀት ሲሞላ ሁኔታዎችን ሁሉ በማስተዋል ተጋፍጦ ከነገሮች በላይ አሸናፊ ይሆናል፡፡
ሰው የቃሉ እውቀት ከሌላው ቅድሚያ መስጠትን አያውቅም፡፡
የህይወት ስኬት የሚለካው በህይወት ቅድሚያ መስጠትን በማወቅ ላይ ነው፡፡ ለምን ቅድሚያ መስጠት እንዳለብን ካወቅንና የህይወት ሃላፊነቶችን ሁሉ በቦታ በቦታቸው ካስቀመጥናቸው አሸናፊ መሆን እንችላለን፡፡ የእግዚአብሄር ቃል እውቀት የሌለው ሰው ግን የቱን ከየቱ እንደሚያደርገው ስለማያውቅ ሃይሉን በማይገባ ጥቃቅን ነገር ላይ ያባክንና ሃይሉን ማጥፋት ባለበት ነገር ላይ የሚገባውን ሳያደርግ ይቀራል፡፡
እንግዲህ፦ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። ማቴዎስ 6፡31-33
እውቀት የሌለው ሰው ለምን እንደተጠራ አያውቅም፡፡
እውቀት የሌለው ሰው እግዚአብሄር ለምን እንደጠራው ስለማይረዳ ሁሉም ውስጥ በመግባት ጉልበሩን ሲጨርስ ይኖራል፡፡ የሰው ጉልበት ውስን ነው፡፡ ሰው ሁሉንም ነገር ለማድረግ ከሞከረ ምንም ነገር ሳያደርግ ይቀራል፡፡ የቃሉ አውቀት የሚያስፈልገው እግዚአብሄር ለምን እንደጠራን እንድናውቅ ነው፡፡ ለምን እንደተጠራ የሚያውቅ ሰው በአትኩሮት የህይወት ሩጫን በሚገባ መሮጥ እና መፈፀም ይችላል፡፡ ለምን እንደተጠራ የሚያውቅ ሰው ግቡን እስኪመታ አያርፍም፡፡ የቃሉ እውቀት ያለው ሰው አላማውን ከግብ ሲያደርሷ ያርፋል በህይወቱም ይደሰታል፡፡   
የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ። ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን . . . ታውቁ ዘንድ ነው፤ ኤፌሶን 1፡17-19
መልካሙን ገድል ተጋድዬአለሁ፥ ሩጫውን ጨርሼአለሁ፥ ሃይማኖትን ጠብቄአለሁ፤2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 4፡7
እውቀት የጎደለው ሰው በእግዚአብሄር ፊት ያለውን የክብር ደረጃ አይረዳም፡፡
በእግዚአብሄር ያለንን ቦታ ማወቃችን ካለፉክክር ሌሎችን እንድናገለግል ይረዳናል፡፡ በእግዚአብሄር ዘንድ ያለውን ቦታ ያልተረዳ ሰው እግዚአብሄር አክብሮት እያለ ቦታውን ከፍ ለማድርግ ህይወቱን በከንቱ ይፈጃል፡፡ በእግዚአብሄር ያለውን የክብር ቦታ የማያውቅ ሰው ማንንም ማገልገል ሳይችል በምስኪንነት አስተሳሰብ ራሱን ብቻ በማገልገል ላይ ተጠምዶ ራሱን ያባክናል፡፡ ኢየሱስ በምድር ላይ ትሁት ሆኖ ለእግዚአብሄር አብ እስከሞት ድረስ በሚገባ እንዲታዘዝ ያደረገው ማንነቱን ማወቁ ነው፡፡     
ኢየሱስ አብ ሁሉን በልጁ እንደ ሰጠው ከእግዚአብሔርም እንደ ወጣ ወደ እግዚአብሔርም እንዲሄድ አውቆ፥ ከእራት ተነሣ ልብሱንም አኖረ፥ ማበሻም ጨርቅ ወስዶ ታጠቀ፤ ዮሃንስ 13፡3-4
እውቀት የጎደለው ሃብታም ሰው ሃብታም ለመሆን በከንቱ ይጥራል፡፡
እውቀት የሌላው ሰው በሁሉ ባለጠጋ ተደርጎ ሳለ ሃብታም ለመሆን በሚደረግ ጥረት በአልባሌ ነገር ህይወቱን ይፈጃል፡፡ ስለ እረኛው በቂ እውቀት የሌለው ሰው ያጣው ነገር እንዳለ ስለሚሰማው ያንን ነገር ለማሟላት እግዚአብሄር የሰጠውን የህይወት ሃላፊነት ይተዋል፡፡ እውቀት የጎደለው ሰው ያለውን የርስት ክብር ስለማይረዳ የሚያልፍ የምድር ርስት ለማከማቸት ቅድሚያ በመስጠት ህይወቱን ያባክናል፡፡
የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ። ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ . . . በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን . . . ታውቁ ዘንድ ነው፤ ኤፌሶን 1፡17-19
እውቀት የጎደለው ሰው በተሰጠው ሃይል መጠቀም ያቅተዋል፡፡
ኢየሱስን አዳኙ አድርጎ የተቀበለ ሰው ሁሉ የእግዚአብሄር ታላቅ ሃይል በውስጡ ይኖራል፡፡ ሰው ግን በውስጡ ያለውን ሃይል ካልተረዳ በድካምና በሽንፈት ሊኖር ይችላል፡፡ እግዚአብሄር የሁሉ አሸናፊ አድርጎት እያለ ካላወቀ በሁሉ ተሸንፎ ይኖራል፡፡
የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ። ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ . . . ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤ ኤፌሶን 1፡17-19
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እውቀት #ጥበብ #ነፍስ #መዳን #ኢየሱስ #ጌታ #እግዚአብሔር #እውቀት #ቅድሚያ #መታዘዝ #ርስት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ባለጠግነት #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ሃይል #ጥሪ #ክብር #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #አእምሮ #ሰላም #ማስተዋል #ልጅ

No comments:

Post a Comment