Popular Posts

Saturday, April 9, 2016

እመን ብቻ እንጂ አትፍራ!


በክርስትና ጉዞ እግዚአብሄር ወዳየልን የህይወት ስፍራ ለመግባትና የእግዚአብሄርን አላማ ፈፅመን እርሱን ለማክበር እንዳንችል የሚያስፈራሩ ከጉዞዋችን ሊያስቀሩን የሚመጡ ብዙ ነገሮች አሉ፡፡

እነዚህን ብዙ ነገሮች መስማትና መከተል እንደሌለብን ይልቁንም ማድረግ ያለብንን እየሱስ እንዲህ በማለት ይገልፀዋል፡፡ 

እመን ብቻ እንጂ አትፍራ

በህይወታችን ጊዜያችንንና ጉልበታችንን ልንሰጠው የማይገባው ነገር ፍርሃት ነው፡፡ በልባችን ስፍራ ልንሰጠው የማይገባው ነገር ጭንቀትና ፍርሃት ነው፡፡ 

በህይወታችን ደግሞ ጊዜያችንን ልናሳልፍበትና በትጋት ልንገነባው የሚገባው ነገር እምነትን ነው፡፡በህይወታችን ትኩረት ልንሰጠው የሚገባ ነገር እምነት የሚመጣበትን የእግዚአብሄርን ቃል መስማት ነው፡፡  በህይወታችን ልንመካበት ደስ ልንሰኝበት ልንጓደድበት የሚገባው ነገር እግዚአብሄር ለእኛ ያለውን ፈቃዱን ነው፡፡ በህይወታችን ልባችንን ልንጥልበት በሙሉ ልባችን ተስፋ ልናደርገው የሚገባው ነገር የእግዚአብሄርን ቃል ነው፡፡

ከእኛ የሚጠበቀው ነገር ሌሎቹንእኛን ስማን ተከተለንካለበለዚያ “ወዮልህ ጠፋህ ተበላህ” የሚሉትን ብዙ ድምፆች ትተን እግዚአብሄር  ስለህይወታችን ያለውን አላማ በቃሉ በማግኘት ቃሉን መቀበልና በእምነት መኖር ብቻ ነው ፡፡

እመን ብቻ እንጂ አትፍራ፡፡ ማርቆስ 536

እግዚአብሄር ለልጆቹ ለእኛ ያዘጋጀውን ከቃሉ ተረድተን እንደቃሉ በእምነት ከቀረብነው እግዚአብሄር ባለጠጋ ነው፡፡ ለሁላችን የሚበቃ ሃብት አለው፡፡ የሃብትና የአቅርቦት ችግር የለበትም፡፡ እግዚአብሄር ግን እንደልጅ በእምነትና በድፍረት እንድንቀርበው ይፈልጋል፡፡

በአይሁዳዊና በግሪክ ሰው መካከል ልዩነት የለምና፤ አንዱ ጌታ የሁሉ ጌታ ነውና፥ ለሚጠሩትም ሁሉ ባለ ጠጋ ነው፤ ሮሜ 10፡12

እመን ብቻ እንጂ አትፍራ፡፡


No comments:

Post a Comment