Popular Posts

Sunday, April 3, 2016

በኃይልና በብርታት አይደለም!

መልሶም፦ ለዘሩባቤል የተባለው የእግዚአብሔር ቃል ይህ ነው። በመንፈሴ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥ ይላል የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር፡፡ዘካርያስ 4:6

    v  አንድን ነገር እንድታደርግለት እግዚአብሄር እንዳዘዘህ ተሰምቶህ ይሆን ?
    v  በአንድ አቅጣጫ እንድትሄድ እግዚአብሄ ተናግሮህ ይሆን ?
    v  አንድ ነገር ማድረግ እንዳለብህ አውቀህ ማረጋገጫውንም ከጌታ አግኝተህ ይሆን?

መልካም ደረጃ ላይ ደርሰሃል ፡፡ እግዚአብሄር እንድትሰራለት የፈለገውን ነገር ማወቅ በጣም አስፈላጊው እርምጃ ነው፡፡ ፈቃዱን እንድታውቅ እግዚአብሄር ረድቶሃል፡፡ እግዚአብሄርን ስለዚህ አመስግን፡፡

አሁንም ይህንን ያየኸውን ነገር እንድትፈፅም እግዚአበሄር ራሱ ዝርዝር ምሪቶችን ሊሰጥህ ይፈልጋል፡፡ ባሳየህ መንገድም መሄድ እንድትችል የሚያበረታህም እርሱ ራሱ ነው፡፡

አንዳንድ ሰዎች የእግዚአብሄርን ፈቃድ ካወቁ በኋላ እግዚአብሄር እንደማያስፈልጋቸው ይመስቸዋል፡፡ ያንንም ያሳያቸውን በራሳቸው ለመፈፀም ሲጥሩ ራሳቸውን አላስፈላጊ ጭንቀት ውስጥ ይጨምራሉ፡፡ በእያንዳንዱ የመታዘዝ ህይወትህ እርምጃ እግዚአብሄር ያስፈልግሃል!

ለህይወትህ ያለውን የእግዚአብሄርን ፈቃድ ስታውቅ ሁሉንም ነገር ከእግዚአብሄር አትረከበውም፡፡

የእግዚአብሄር እርዳታ ፈቃዱን በማሳየት ይጀምራል እንጂ  በዚያ ላይ አያበቃም፡፡

እግዚአብሄር በእርምጃህ ሁሉ ሊረዳህ ካንተ ጋር ስላለ ተረጋጋ፡፡ ዝርዝር ቅድመ ሁኔታዎችን እንዲያሳይህ በፀሎት ምሪቱን ጠብቅ፡፡ ከ ፈቃድ ለህይወትህ ያሳየህ እግዚአብሄር ፈቃዱ በተግባር እንዴት እንደሚተረጎም ደግሞ ያሳይሃል፡፡ በዚያ ባሳየህ መንገድ እንድትሄድ ሃይልን ያስታጥቅሃል ያበረታሃል፡፡

ፈቃዱን የሚያሳይህ እርሱ ነው፡፡ በውስጥህም የሚፈፅመው እርሱ ነው፡፡

ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን። ሮሜ 11፡36

ተጀምሮ እስከሚጨረስ ድረስ በመንፈሱ እንጂ በኃይልና በብርታት አይደለም፥



No comments:

Post a Comment