I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር ክፍል 3 እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ...
-
ኢኮኖሚ ምጣኔ ሀብት ነው፡፡ ሀብት ውስን ነው። የምጣኔ ሀብት ጥናት ውስን የሆነውን ሀብት መጥኖ ስለመጠቀም ያስተምራል፡፡ ውስን የሆነውን ሀብት ቅድሚያ ለሚሰጠው ...
-
እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ። 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ...
-
https://youtu.be/Vy_MmJQ7AUg
-
ብልፅግና የሚመነጨው ከእግዚአብሄር ሲሆን ድህነት የሚመነጨው ከሰይጣን ነው፡፡ ድህነትም ብልፅግናም የሚያልፈው በሰው አእምሮ ነው፡፡ ሰው የሚበለፅገው አእምሮው ነው፡፡ አእምሮው የበለፀገ ሰው ደሃ መሆን አይችልም፡፡ አእ...
-
እግዚአብሔ ሔር የአላማ አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሔር የሚወደው እና የማይወደው የተለየ ነገር አለ፡፡ እግዚአብሔር ለህይወታችን የሚፈልገው እና የማይፈልገው ነገር አለ፡፡ እግዚአብሔር ለህይወታችን ያቀደው የተለየ እቅድ አለ...
-
እግዚአብሔርን የምንሰማባቸው ሶስት አይነት ድምፆች ይገኛሉ፡፡ እግዚአብሔር በዋነኝነት በሶስት መንገዶች ለራሳችን ይናገረናል ፡፡ የህሊና ድምፅ የውስጥ ምስክርነት የውስጥ ድምፅ እና የመንፈስ ቅዱስ ድምፅ በሚባሉ ሶ...
-
ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር ክፍል 4 እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ...
Thursday, September 19, 2024
ዕራቁትህን እንደ ሆንህ ማን ነገረህ?
Thursday, September 12, 2024
መስከረም አንድን ከጷጉሜ አምስት የሚለየው
ህይወት በፍጹም ከባድ ሸክም መሆን የለበትም።
እናንተ ደካሞች ሸክማችሁ የከበደ ሁሉ፥ ወደ እኔ ኑ፥ እኔም አሳርፋችኋለሁ። ቀንበሬን በላያችሁ ተሸከሙ ከእኔም ተማሩ፥ እኔ የዋህ በልቤም ትሑት ነኝና፥ ለነፍሳችሁም ዕረፍት ታገኛላችሁ፤ ቀንበሬ ልዝብ ሸክሜም ቀሊል ነውና። የማቴዎስ ወንጌል 11፥28-30
ህይወትን ታዲያ መልካም የሚያደርገው ወደ ክርስቶስ መምጣታችን ነው። ክርስቶስ ከሌለበት መስከረም 1 ይልቅ ክርስቶስ ያለበት ጷጉሜ 5 ይሻላል የሚባልው ለዚያ ነው።
ጥል ባለበት ዘንድ እርድ ከሞላበት ቤት በጸጥታ ደረቅ ቍራሽ ይሻላል። መጽሐፈ ምሳሌ 17፥1
ካለ ክርስቶስ ከምንኖረው መስከረም አንድ ይልቅ በክርስቶስ የተገለጠውን የእግዚአብሄርን ፍቅር ተቀብለን የምንኖርበት ጷጉሜ 5 ይሻላል።
በልጁ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፤ በልጁ የማያምን ግን የእግዚአብሔር ቍጣ በእርሱ ላይ ይኖራል እንጂ ሕይወትን አያይም። የዮሐንስ ወንጌል 3፥36
ክርስቶስ በህይወታችን ካለ የህይወት ከፍታው እና ዝቅታው ሁሉ ይጣፍጣል። ክርስቶስን ካልተከተልን ግን መስከረም አንድ ትርጉም የለሽ የከባድ ሸክም ሕይወት ይሆናል።
ከአእላፍ ይልቅ በአደባባዮችህ አንዲት ቀን ትሻላለች፤ በኃጥኣን ድንኳኖች ከመቀመጥ ይልቅ፥ በእግዚአብሔር ቤት እጣል ዘንድ መረጥሁ። መዝሙረ ዳዊት 84፥10
ቀኑን ወሩን እና አመቱን የሚያቀለው የሚያደርገው እና የሚጠቅመው ብቸኛው ነገር በክርስቶስ መሆን ብቻ ነው።
በክርስቶስ ኢየሱስ አዲስ ፍጥረት መሆን ይጠቅማል እንጂ መገረዝ ቢሆን ወይም አለመገረዝ አይጠቅምምና። ወደ ገላትያ ሰዎች 6፥15
መልካም አዲስ አመት
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
#ሀበሻ #ዝግ #እግዚአብሔርንመምሰል #ኢየሱስ #ጌታ #ምልጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ምስጋና #እምነት #አበሻ #አማርኛ #ሰላም #ደስታ #አዲስአመት #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ኢትዮጲያ #ፀሎት
Wednesday, September 11, 2024
መልካም አዲስ ዘመን
Tuesday, September 10, 2024
መልካም አዲስ መንፈስ
ክርስቶስን እንደ አዳኝ እና ጌታ ስንቀበል የእግዚአብሄር መንፈስ በእኛ ውስጥ መኖር ይጀምራል። ታዲያ ህይወታችንን አዲስ የሚያደርገው በክርስቶስ የምንቀበለው አዲስ መንፈስ ነው።
የክርስቶስ መንፈስ በውስጡ የማይኖር ሰው የክርስቶስ ወገን አይደለም።
እናንተ ግን የእግዚአብሔር መንፈስ በእናንተ ዘንድ ቢኖር፥ በመንፈስ እንጂ በሥጋ አይደላችሁም። የክርስቶስ መንፈስ የሌለው ከሆነ ግን ይኸው የእርሱ ወገን አይደለም። ወደ ሮሜ ሰዎች 8፥9
ከሃጢያታችን አጥቦ ለእግዚአብሄር ልጅነት ያበቃን የእግዚአብሄር መንፈስ ነው።
እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም፤ ወደ ቲቶ 3፥5
ህይወታችንን የሚያድሰው የእግዚአብሄር መንፈስ ብቻ ነው።
አዲስ አመትን መጠበቅ መልካም ነው እውነትኛ አዲስ አመት የሚገኘው በክርስቶስ ህይወት ብቻ ነው። አሁንም ክርስቶስን ብንቀበል አዲስ ቀን አዲስ ወር አዲስ አመት በአጠቃላይ አዲስ ህይወት ይሆንልናል።
መልካም አዲስ አመት
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
#ሀበሻ #ዝግ #እግዚአብሔርንመምሰል #ኢየሱስ #ጌታ #ምልጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ምስጋና #እምነት #አበሻ #አማርኛ #ሰላም #ደስታ #አዲስአመት #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ኢትዮጲያ #ፀሎት
Monday, September 9, 2024
መልካም አዲስ ህይወት
Saturday, September 7, 2024
መልካም አዲስ ልብ
መልካም አዲስ ቤተሰብ
Friday, September 6, 2024
መልካም አዲስ መንግስት
ክርስቶስ ኢየሱስ ስለሃጢያታችን በመስቀል ላይ እንደተሰቀለ እና እንደሞተ ብናምን እንዲሁም ሞትንም ድል አድርጎ በሶስተኛው ቀን እንደተነሳ ብንመሰክር ከጨለማ ሥልጣን በመዳን ወደ እግዚአብሔር የፍቅሩ ልጅ መንግሥት እንፈልሳለን።
እርሱ ከጨለማ ሥልጣን አዳነን፥ ቤዛነቱንም እርሱንም የኃጢአትን ስርየት ወዳገኘንበት ወደ ፍቅሩ ልጅ መንግሥት አፈለሰን። ወደ ቆላስይስ ሰዎች 1፥13-14
ክርስቶስ ኢየሱስን ታችን አድርገን ከመቀበላችን በፊት ሁላችንም በሰይጣን መንግስት ግዛት ስር ነበርን። ኢየሱስን በተቀበልንበት ቅጽበት ከጨለማው ስልጣን አምልጠን ወደ እግዚአብሔር መንግስት ተዘዋውረናል።
በበደላችሁና በኃጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ፤ በእነርሱም፥ በዚህ ዓለም እንዳለው ኑሮ፥ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ እንደ ሆነው በአየር ላይ ሥልጣን እንዳለው አለቃ ፈቃድ፥ በፊት ተመላለሳችሁባቸው። በእነዚህም ልጆች መካከል እኛ ሁላችን ደግሞ፥ የሥጋችንንና የልቡናችንን ፈቃድ እያደረግን፥ በሥጋችን ምኞት በፊት እንኖር ነበርን እንደ ሌሎቹም ደግሞ ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነበርን። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2፥1-3
ክርስቶስን ሳንቀበል በጨለማው መንግስት ውስጥ እየኖሩ ቀኑ በመለወጡ ብቻ እውነተኛ አዲስ አመት ይሆንልናል ብሎ መጠበቅ ሞኝነት ነው። አዲሱን አመት እውነተኛ አዲስ አመት የሚያደርገው በክርስቶስ በመሆን ወደ እግዚአብሔር የፍቅር መንግስት መፍለስ ብቻ ነው።
መልካም አዲስ አመት
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
#ሀበሻ #ዝግ #እግዚአብሔርንመምሰል #ኢየሱስ #ጌታ #ምልጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ምስጋና #እምነት #አበሻ #አማርኛ #ሰላም #ደስታ #አዲስአመት #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ኢትዮጲያ #ፀሎት
Thursday, September 5, 2024
መልካም አዲስ ፍጥረት