Popular Posts

Saturday, October 28, 2017

ለራሳቸው እንዳይኖሩ

ከእኛ አንድ ስንኳ ለራሱ የሚኖር የለምና፥ ለራሱም የሚሞት የለም፤ ሮሜ 14:7
በሕይወትም ያሉት ስለ እነርሱ ለሞተውና ለተነሣው እንጂ ወደ ፊት ለራሳቸው እንዳይኖሩ ስለ ሁሉ ሞተ። 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡15
ኢየሱስ የሞተልን ንስሃ ገብተን የራሳችንን ህይወት ካቆምንበት እንድንቀጥል አይደለም፡፡ ኢየሱስ የሞተው እኛ ለራሳችን እንድንሞት ነው፡፡ ኢየሱስ የሞተው ለእርሲ እንድንኖርለት ነው፡፡
በክርስትና ስኬታማ የምንሆነው ለራሳችን ስንኖር ሳይሆን ለራሳችን ስንሞት ነው፡፡ በክርስትና የምንከናወነው ለሞተልን ለእርሱ ስንኖር ነው፡፡
ነፍሱን ሊያድን የሚወድ ሁሉ ያጠፋታልና፤ ስለ እኔ ነፍሱን የሚያጠፋ ሁሉ ግን እርሱ ያድናታል። ሉቃስ 9፡24
ነፍሱን ሊያስደስት የሚወድ ፣ ለነፍሱ ስሜት ቅድሚያ የሚሰጥና ነፍሱን በዋነኝነት የሚያከብር ሰው ለሞተለት ለክርስቶስ መኖር አይችልም፡፡
ነገር ግን ሩጫዬንና ከጌታ ከኢየሱስ የተቀበልሁትን አገልግሎት እርሱም የእግዚአብሔርን ጸጋ ወንጌልን መመስከር እፈጽም ዘንድ ነፍሴን በእኔ ዘንድ እንደማትከብር እንደ ከንቱ ነገር እቆጥራለሁ። ሐዋርያት 20፡24
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እምነት #ማየት #ነፍሱን #የሚያጠፋ #ሞተ #እንዲኖሩ #እንዳይኖሩ #የሚኖር #የሚሞት #መከተል #ቃል #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #ደቀመዝሙር #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ነፍስንመካድ #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ  

No comments:

Post a Comment