Popular Posts

Monday, May 25, 2020

የደስታ ያለህ

ክርስቲያናዊ ደስታን አፈላለግ በሚቀጥሉት አምስት እምነቶች ላይ የተገነባ የህይወት መረዳት ነው፡፡

l. ደስተኛ ለመሆን መጓጓት አለም አቀፋዊ ሁለንተናዊ የሰዎች ምኞት ነው፡፡ ደስተኛ ለመሆን የመመኘት ልምምድ መልካም እና ምንም ክፋት የሌለበት ነገር ነው፡፡

2. መጥፎ ስሜት ይመስል ደስተኛ የመሆን ምኞታችንን ለመካድ ወይም ለመቃወም በፍጹም መሞከር የለብንም፡፡ ይልቁን ጥልቅ እና በጣም ዘላቂ እርካታን ለማግኘት ይህንን ምኞት ማጠንከር እና ማዳበር አለብን፡፡

3. እጅግ ጥልቅ እና ዘላቂ ደስታ የሚገኘው በእግዚአብሄር ውስጥ ብቻ ነው፡፡

4. በእግዚአብሔር የምናገኘው ደስታ ከሌሎች ጋር በፍቅር ሲጋራ ወደ ደስታ ፍጻሜ ይደርሳል፡፡

5. የራሳችንን ደስታ ለማሳደድን እስከሞከርን ጊዜ ድረስ ግን እግዚአብሄርን ማክበርና ሰውን መውደድ ያቅተናል፡፡ 

በሌላ አነጋገር የሰው ልጅ ዋናው ፍፃሜ በእግዚአብሄር ለዘላለም ደስ በመሰኘት እርሱን ማክበር ነው፡፡ 

From the Book Desiring God by John Piper Page 16.


Wednesday, May 13, 2020

ስጡ


ስጡ ይሰጣችሁማል፤ በምትሰፍሩበት መስፈሪያ ተመልሶ ይሰፈርላችኋልና፥ የተጨቈነና የተነቀነቀ የተትረፈረፈም መልካም መስፈሪያ በእቅፋችሁ ይሰጣችኋል። የሉቃስ ወንጌል 638

ይህ የኢየሱስ ንግግር ስለመስጠት እንጂ ስለ መቀበል የተደረገ ንግግር አይደለም፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች ይህን ክፍል ስለመቀበል ይሰብኩታል፡፡ የዚህ የመስጠት ትምህርት አላማ ግን መስጠት እንጂ በፍፁም መቀበል አይደለም፡፡

ሰው ሲሰጥ ወደ አእምሮው የሚመጣ ጥያቄ አለ፡፡ ስሰጥ እኔስ ቢጎድልብኝ የሚል ጥያቄ በሁላችንም አእምሮ ውስጥ ይመላለሳል፡፡

ሰጥቼ እኔስ ቢጎድልብኝ የሚለው ጥያቄ የሚፈጠርብን ምክኒያት ገንዘብ ጊዜያዊም ቢሆን የመተማመን ስሜትን ስለሚሰጠን ነው፡፡  

በአጠቃላይ አለምን የሚያንቀሳቅሰው የእግዚአብሄር ፍቅር ወይም የገንዘብ ማጣት ፍርሃት ነው፡፡ ሰው እንዳያጣ ብዙ ነገሮችን ያደርጋል፡፡

እንግዲህ፦ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። የማቴዎስ ወንጌል 6፡31-32

ሰው ገንዘቡን ለመስጠት የሚገዳደረው ምክኒያት ገንዘብ የመተማመን ስሜትን በሰው ውስጥ ስለሚፈጥር ነው፡፡  

ታዲያ ገንዘባችንን ስንሰጥ የምንሰጠው መተማመኛችንን ነው፡፡ ገንዘባችንን ለመስጠት ከገንዘብ በላይ የምንተማመንበት እግዚአብሄርን ማመን ይጠይቃል፡፡ ገንዘብ ለመስጠት ከሚታየው ያለፈ የእግዚአብሄርን መንግስት አሰራር በእምነት አይን ማየት ይጠይቃል፡፡ ገንዘብን ለመስጠት የእግዚአብሄርን ቃል ማመን ይጠይቃል፡፡  

ለዘሪ ዘርን ለመብላትም እንጀራን በብዙ የሚሰጥ እርሱም የምትዘሩትን ዘር ይሰጣችኋል ያበረክትላችሁማል፥ የጽድቃችሁንም ፍሬ ያሳድጋል፤ 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9፡10

ስጡ ብሎ ኢየሱስ ይሰጣችኋል ያለበት ምክኒያት በሰው ውስጥ የሚነሳውን ሰጥቼ ቢጎድልብኝስ? የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ነው፡፡ ስጡ ብሎ መልሱ ባጣስ ለሚለው ጥያቄ መልሱ ስለሰጣችሁ አይጎድልባችሁም የሚለው ነው፡፡ ስለሰጣችሁ አታጡም ስለሰጣችሁ አትከስሩም፡፡

ይህንም እላለሁ፦ በጥቂት የሚዘራ በጥቂት ደግሞ ያጭዳል፥ በበረከትም የሚዘራ በበረከት ደግሞ ያጭዳል። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9፡6

ስትሰጡ ይሰጣችሁዋል፡፡ ስትሰጡ ይጨመርላችሁዋል፡፡ ስትሰጡ ይበልጥ ይሰጣችሁዋል፡፡

ስጡ ይሰጣችሁማል፤ በምትሰፍሩበት መስፈሪያ ተመልሶ ይሰፈርላችኋልና፥ የተጨቈነና የተነቀነቀ የተትረፈረፈም መልካም መስፈሪያ በእቅፋችሁ ይሰጣችኋል። የሉቃስ ወንጌል 6፡38

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እረፍት #ቅድሚያ #እምነት #መደገፍ #ሰንበት #መዝራት #ማጨድ #ፅድቁን #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ጌታ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #እምነት #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ምህረት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ


Thursday, May 7, 2020

Blessed


Blessed are those who can say like Caleb “I am just as vigorous to go out to battle now as I was then”.

I am still as strong today as the day Moses sent me out; I am just as vigorous to go out to battle now as I was then. Joshua 14:11

Caleb is a good example of perseverance. He is a good example of not giving up. He is a good example of not being affected by different life situations.

He has seen in the lows and the highs. He has seen the yes's and the no's. He has seen success and failure. He has seen progress and setbacks.

Those life situations were not good enough to make him quit. He just continued.

All the life situations were not good excuses to give up.

Instead, all life situations taught him that they don't really matter. The more he passes through the life situations he came across, he could put them in their right places.

I know what it is to be in need, and I know what it is to have plenty. I have learned the secret of being content in any and every situation, whether well-fed or hungry, whether living in plenty or in want. Philippians 4:12

Instead of all the life challenges makes him loses his passion to achieve more. They taught him that the only thing that matters is God himself.

Blessed are those who can say like Caleb “I am just as vigorous to go out to battle now as I was then”.
Abiy Wakuma Dinsa
For More Articles https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
#God #Jesus #knowledge #rejoice # perseverance #trustgod #grace #salvation #church #testimony #rejoice #preaching #Bible #theword #Abiydinsa #scriptures #abiywakumadinsa