I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
If you had it to do over again, you’d marry me for love Love and Let Live Love and Let Live By Dale Carnegie How To Win Friends And I...
-
ወደ ውጭም አውጥቶ፦ ጌቶች ሆይ፥ እድን ዘንድ ምን ማድረግ ይገባኛል ? ኣላቸው። የሐዋርያት ሥራ 16:30 ይህ የብዙ ሰው የልብ ጨኸት ነው፡፡ ይህ በህይወት ዘመን ሊመለስ የሚገባው ወሳኝ ጥያቄ ...
-
Enjoying the goodness of the Lord in every moment of my life.
-
ምስክርነት በአቢይ ዋቁማ ዲንሳ Witnessing Abiy Wakuma Dinsa
-
ሰው የተፈጠረው በእግዚአብሄር መልክና አምሳል ነው፡፡የሰው መኖሪያ ቤቱ እና ስጋው ከምድር አፈር ቢበጅም ሰው ግን አፈር አይደለም፡፡ ሰው በእግዚአብሄር አምሳል የተፈጠረ በስጋ ውስጥ የሚኖረው መንፈስ ነው፡፡ እግዚአ...
-
We are a part of generations. We build a foundation for the next generation and we actually shape it in what we say and do. We co...
-
የእግዚአብሔር ቃል ቅን ነውና ሥራውም ሁሉ በእምነት ነውና። መዝሙር 33፡4 እግዚአብሄር ቅን ነው፡፡ የእግዚአብሄርም ቃል ቅን ነው፡፡ የእግዚአብሄ ቃል ቀጥተኛ ነው፡፡ የእግዚአብሄር ቃል እንዳለ ሊቀበሉት...
Wednesday, October 30, 2024
የአሜሪካ የፕሬዝዳንታዊነት ምርጫ
Tuesday, October 29, 2024
ሀሎዊን ክፍል 2
ሃሎዊን Halloween የሚባለው በአል በኦክቶበር ወር መጨረሻ ላይ በተለያየ መልኩ ይከበራል፤ ባብዛኛው ህዝብ ዘንድ እንደ አንድ ባህል የሚከብረው ይህ የሃሎዊን በአል ሰዎች ቢገባቸውም ባይገባቸውም መንፈሳዊ እንደምታ የለውም ማለት ግን አይቻልም።
ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ እንጂ ስለሌላ አይመጣም የተባለው ጠላት ዲያቢሎስ ባገኘው አጋጣሚ የሰዎችን ህይወት ይሰርቃል ያርዳል ያጠፋል።
ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ። የዮሐንስ ወንጌል 10፣10
ሰይጣን በእግዚአብሄር ይፈጠር የእግዚአብሄር መላክ የነበር ሳጥናኤል ነበር። ሳጥናኤል ሰይጣን የሆነው እና እርሱን ከተከተሉት የወደቁት መላእክት ጋር ከእግዚአብሄር ፊት ወደ ምድር የተጣለው በትእቢት እንደ እግዚአብሄር ሊሆን ስለፈለገ ነበር።
መኖሪያቸውንም የተዉትን እንጂ የራሳቸውን አለቅነት ያልጠበቁትን መላእክት በዘላለም እስራት ከጨለማ በታች እስከ ታላቁ ቀን ፍርድ ድረስ ጠብቆአቸዋል። የይሁዳ መልእክት 1:6
ሰይጣን ዲያብሎስ የእሳት ባህር ቅጣት ተዘጋጅቶልታል።
እስክዚያ ግን የቻለውን ያህል ሰው አታልሎ ብዙ ሰዎችን ወደ እሳት ባህር መሄድ ይፈልጋል። የእሳት ባህር ለሰው ያልተዘጋጀ ቢሆንም እግዚአብሄር በክርስቶስ ኢየሱስ ያዘጋጀውን ከሃጢያት የመዳኛ መንገድ ያልተቀበሉ ሁሉ ለሰይጣን እና ለመላእክቱ ወደተዘጋጀው የእሳት ባህር ይጣላሉ።
እግዚአብሄር በክርስቶስ ኢየሱስ ያዘጋጀውን ከሃጢያት የመዳኛ መንገድ የተቀብሉ ብቻ ከእግዚአብሄር ጋር ለዘላለም አይለያዩም ለሰይጣን እና ለመላእክቱ ወደተዘጋጀው የእሳት ባህር አይጣሉ።
በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ። የማቴዎስ ወንጌል 25:11
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
#ሰይጣን #ሀሎዊን #ሃሎዊን #ጠላት #ዲያቢሎስ #አቢይዋቁማ #ኢየሱስጌታ #ኢየሱስ