I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
God created mankind simple. He created him and commanded him to eat everything except the tree of the knowledge of good and evil. But m...
-
We want God to use us mightily. We ask God “use me and I will do whatever it takes”. When the time to pay the price that isn’t expected...
-
በእግዚአብሔር ቅንዓት እቀናላችኋለሁና፥ እንደ ንጽሕት ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ አጭቻችኋለሁና፤ ነገር ግን እባብ በተንኮሉ ሔዋንን እንዳሳታት፥ አሳባችሁ ተበላሽቶ ...
-
አቢይ ጥሞና #አንድ አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። የማቴዎስ ወንጌል 6፡33 ሰው የተፈጠረው ለእግዚአብሄ...
-
Believe God exists And without faith, it is impossible to please God because anyone who comes to him must believe that he exists and that ...
-
We are created by God for a specific purpose. We are created in His glory. We are not here by accident. We are created on purpose. W...
-
Singleness is a Blessing Classifying establishment according to marital status is false teaching. And one of the problems of society is t...
Wednesday, October 30, 2024
የአሜሪካ የፕሬዝዳንታዊነት ምርጫ
Tuesday, October 29, 2024
ሀሎዊን ክፍል 2
ሃሎዊን Halloween የሚባለው በአል በኦክቶበር ወር መጨረሻ ላይ በተለያየ መልኩ ይከበራል፤ ባብዛኛው ህዝብ ዘንድ እንደ አንድ ባህል የሚከብረው ይህ የሃሎዊን በአል ሰዎች ቢገባቸውም ባይገባቸውም መንፈሳዊ እንደምታ የለውም ማለት ግን አይቻልም።
ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ እንጂ ስለሌላ አይመጣም የተባለው ጠላት ዲያቢሎስ ባገኘው አጋጣሚ የሰዎችን ህይወት ይሰርቃል ያርዳል ያጠፋል።
ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ። የዮሐንስ ወንጌል 10፣10
ሰይጣን በእግዚአብሄር ይፈጠር የእግዚአብሄር መላክ የነበር ሳጥናኤል ነበር። ሳጥናኤል ሰይጣን የሆነው እና እርሱን ከተከተሉት የወደቁት መላእክት ጋር ከእግዚአብሄር ፊት ወደ ምድር የተጣለው በትእቢት እንደ እግዚአብሄር ሊሆን ስለፈለገ ነበር።
መኖሪያቸውንም የተዉትን እንጂ የራሳቸውን አለቅነት ያልጠበቁትን መላእክት በዘላለም እስራት ከጨለማ በታች እስከ ታላቁ ቀን ፍርድ ድረስ ጠብቆአቸዋል። የይሁዳ መልእክት 1:6
ሰይጣን ዲያብሎስ የእሳት ባህር ቅጣት ተዘጋጅቶልታል።
እስክዚያ ግን የቻለውን ያህል ሰው አታልሎ ብዙ ሰዎችን ወደ እሳት ባህር መሄድ ይፈልጋል። የእሳት ባህር ለሰው ያልተዘጋጀ ቢሆንም እግዚአብሄር በክርስቶስ ኢየሱስ ያዘጋጀውን ከሃጢያት የመዳኛ መንገድ ያልተቀበሉ ሁሉ ለሰይጣን እና ለመላእክቱ ወደተዘጋጀው የእሳት ባህር ይጣላሉ።
እግዚአብሄር በክርስቶስ ኢየሱስ ያዘጋጀውን ከሃጢያት የመዳኛ መንገድ የተቀብሉ ብቻ ከእግዚአብሄር ጋር ለዘላለም አይለያዩም ለሰይጣን እና ለመላእክቱ ወደተዘጋጀው የእሳት ባህር አይጣሉ።
በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ። የማቴዎስ ወንጌል 25:11
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
#ሰይጣን #ሀሎዊን #ሃሎዊን #ጠላት #ዲያቢሎስ #አቢይዋቁማ #ኢየሱስጌታ #ኢየሱስ
.jpeg)
