I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
አንድነት ተመሳሳይነት አይደለም፡፡ አንድነት በአንድ ጣራ ስር መሰብሰብ አይደለም፡፡ አንድነት ተመሳሳይ ነገር ማሰብ እና ማድረግ አይደለም፡፡ አንድነት ተመሳሳይ ስጦታ መኖር አይደለም፡፡ አንድነትን በተመሳሳይነት መ...
-
እግዚአብሄር በመጀመሪያ የፈጠረን በጤንነት ነው፡፡ ከጥንት እግዚአብሄር ሙላትን ፣ ጤንነትን እና ብርታትን እንጂ በሽታንና ደዌን አልፈጠረም፡፡ በማንኛውም ምክኒያት ጤንነታችንን ብናጣና ብን...
-
አንደኛው የእግዚአብሄር ስም ፈዋሽ አምላክ የሚል ነው፡፡ እግዚአብሄር በመፈወስ ይታወቃል፡፡ እግዚአብሄር ሰዎችን ሙሉ በማድረግ ይታወቃል፡፡ ነፍሴ ሆይ፥ እግዚአብሔርን ባርኪ፥ ምስጋናውንም ሁሉ አትርሺ፤ ኃጢአ...
-
ክርስቶስ ስለሃጢያታችን ከቃሉ በመስቀል ላይ እንደሞተ ከቃሉ ስናይ ደህንነታችንን እንቀበላለን፡፡ እንዲሁም ኢየሱስ ስለሃጢያታችን መገረፉን ከልባችን ስንረዳ በሽታ በእኛ ላይ አቅም አይኖረውም፡፡ የሰው ፈውስ በመስቀል ...
-
አስቀድማችሁ ከፈሪሳውያን እርሾ ተጠበቁ! ክፍል 7 ባስተላለፋችሁትም ወግ የእግዚአብሔርን ቃል ትሽራላችሁ፤ እንደዚሁም ይህን የሚመስል ብዙ ነገር ታደርጋላችሁ። የማርቆስ ወንጌል 7፡13 ፈሪሳዊያን እንጅ ታጥቦ ስለ መብላይ...
-
ከዚያ ወዲያ ኢየሱስ ከዲያብሎስ ይፈተን ዘንድ መንፈስ ወደ ምድረ በዳ ወሰደው፥ አርባ ቀንና አርባ ሌሊትም ከጦመ በኋላ ተራበ። ፈታኝም ቀርቦ፦ የእግዚአብሔር ልጅ ከሆንህ፥ እነዚህ ድን...
-
ማሪያም ታማልዳለች ወይስ አታማልድም የሚለው ጥያቄ በኢትዮጲያ ውስጥ ብዙ ክርክርን ሲያስነሳ የቆየ ጥያቄ ነው፡፡ አንዳንዶች ማሪያም በምድር ላይ እያለች አማልዳለች ነገር ግን ከሞተች በኃላ ማማለድ አትችልም ብለው...
-
Love is patient, love is kind. It does not envy, it does not boast, it is not proud. It does not dishonor others, it is not self-seeking, ...
-
እንዲህ ሲል፦ በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ። በዚያችም ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፥ ወደ እርሱም እየመጣች፦ ከባላጋራዬ ፍረድልኝ ትለ...
Wednesday, October 30, 2024
የአሜሪካ የፕሬዝዳንታዊነት ምርጫ
Tuesday, October 29, 2024
ሀሎዊን ክፍል 2
ሃሎዊን Halloween የሚባለው በአል በኦክቶበር ወር መጨረሻ ላይ በተለያየ መልኩ ይከበራል፤ ባብዛኛው ህዝብ ዘንድ እንደ አንድ ባህል የሚከብረው ይህ የሃሎዊን በአል ሰዎች ቢገባቸውም ባይገባቸውም መንፈሳዊ እንደምታ የለውም ማለት ግን አይቻልም።
ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ እንጂ ስለሌላ አይመጣም የተባለው ጠላት ዲያቢሎስ ባገኘው አጋጣሚ የሰዎችን ህይወት ይሰርቃል ያርዳል ያጠፋል።
ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ እኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁ። የዮሐንስ ወንጌል 10፣10
ሰይጣን በእግዚአብሄር ይፈጠር የእግዚአብሄር መላክ የነበር ሳጥናኤል ነበር። ሳጥናኤል ሰይጣን የሆነው እና እርሱን ከተከተሉት የወደቁት መላእክት ጋር ከእግዚአብሄር ፊት ወደ ምድር የተጣለው በትእቢት እንደ እግዚአብሄር ሊሆን ስለፈለገ ነበር።
መኖሪያቸውንም የተዉትን እንጂ የራሳቸውን አለቅነት ያልጠበቁትን መላእክት በዘላለም እስራት ከጨለማ በታች እስከ ታላቁ ቀን ፍርድ ድረስ ጠብቆአቸዋል። የይሁዳ መልእክት 1:6
ሰይጣን ዲያብሎስ የእሳት ባህር ቅጣት ተዘጋጅቶልታል።
እስክዚያ ግን የቻለውን ያህል ሰው አታልሎ ብዙ ሰዎችን ወደ እሳት ባህር መሄድ ይፈልጋል። የእሳት ባህር ለሰው ያልተዘጋጀ ቢሆንም እግዚአብሄር በክርስቶስ ኢየሱስ ያዘጋጀውን ከሃጢያት የመዳኛ መንገድ ያልተቀበሉ ሁሉ ለሰይጣን እና ለመላእክቱ ወደተዘጋጀው የእሳት ባህር ይጣላሉ።
እግዚአብሄር በክርስቶስ ኢየሱስ ያዘጋጀውን ከሃጢያት የመዳኛ መንገድ የተቀብሉ ብቻ ከእግዚአብሄር ጋር ለዘላለም አይለያዩም ለሰይጣን እና ለመላእክቱ ወደተዘጋጀው የእሳት ባህር አይጣሉ።
በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋል፦ እናንተ ርጉማን፥ ለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱ። የማቴዎስ ወንጌል 25:11
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
#ሰይጣን #ሀሎዊን #ሃሎዊን #ጠላት #ዲያቢሎስ #አቢይዋቁማ #ኢየሱስጌታ #ኢየሱስ
.jpeg)
