Popular Posts

Monday, August 19, 2019

መንገድህን እባክህ አሳየኝ


አሁንም በፊትህ ሞገስን አግኝቼ እንደ ሆነ፥ አውቅህ ዘንድ በፊትህም ሞገስን አገኝ ዘንድ መንገድህን እባክህ አሳየኝ፤ ይህም ሕዝብ ሕዝብህ እንደ ሆነ ተመልከት አለው። ኦሪት ዘጸአት 33፡13
መንገድህን እባክህ አሳየኝ ልመና ከእግዚአብሄር መንገድ ውጭ ያለው መንገድ ሁሉ አደገኛ የሆነ የብክነት ህይወት እንደሆነ የተረዳ ሰው የልብ ጩኸት ነው፡፡
አቤቱ፥ መንገድህን አመልክተኝ፥ ፍለጋህንም አስተምረኝ። መዝሙረ ዳዊት 25፡4
መንገድህን እባክህ አሳየኝ የሚለው ጩኸት ህይወቱን ከእግዚአብሄር ፈቃድ ውጭ ላማባከን የማይፈልግ ሰው የልብ ጩኸት ነው፡፡
አቤቱ፥ መንገድህን ምራኝ፥ በእውነትህም እሄዳለሁ፤ ስምህን ለመፍራት ልቤ ደስ ይለዋል።  መዝሙረ ዳዊት 86፡11
መንገድህን እባክህ አሳየኝ የሚለው ጩኸት በእግዚአብሄር መንገድ ብቻ እውነተኛ ስኬት ፍሬማነትና ውጤት እንደሚገኝ የተረዳ ሰው የልብ ጩሸት ነው፡፡
መንገድህን እባክህ አሳየኝ የሚለው ጩኸት ለእያንዳንዳችን የተወሰነ የተለየ መንገድ እንዳለ ሰው ስለሄደበት ብቻ በግርታ መሄድ እንደሌለበት የተረዳ ሰው የልብ ጩኸት ነው፡፡
ለእናንተ የማስባትን አሳብ እኔ አውቃለሁ፤ ፍጻሜና ተስፋ እሰጣችሁ ዘንድ የሰላም አሳብ ነው እንጂ የክፉ ነገር አይደለም። ትንቢተ ኤርምያስ 29፡11
መንገድህን እባክህ አሳየኝ የሚለው ጩኸት እኛ እንዲመራን ከምንፈልገው በላይ እግዚአብሄር ሊመራን እንደሚፈልግ የተረዳ ሰው የልብ ጩኸት ነው፡፡
መንገድህን እባክህ አሳየኝ የሚለው ጩኸት ከእግዚአብሄር መንገድ ውጭ የሆነው የእኛ መንገድ የትም የማያደረስ የድካምና እና የከንቱነት መንገድ እንደሆነ የተረዳ ሰው ጩኸት ነው፡፡
መንገድህን እባክህ አሳየኝ የሚለው ጩኸት ለመሄድ ብቻ ብሎ እግዚአብሄር በሌለበት መንገድ ከመሄድ አለመሄድ መቅረት እንደሚሻል የተረዳ ሰው የልብ ጩኸት ነው፡፡
እርሱም፦ አንተ ከእኛ ጋር ካልወጣህስ፥ ከዚህ አታውጣን። ኦሪት ዘጸአት 33፡15
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር   share ያድርጉ!
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ምሪት #መንገድ #ድምፅ #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment