Popular Posts

Saturday, October 1, 2022

 

አእምሮን የሚያልፍ
በእርሱ ከታመንን ከአካባቢያችን ጩኽትና ረብሻ ከፍ ያለ አእምሮን የሚያልፍ ሰላም እንደምናገኝ መፅሀፍ ቅዱስ ይናገራል:: ህይወታችን ሁልጊዜ ጥርት ያለ ቀጥታ መስመር እይደለም:: በህይወታችን ያለውን ነገር ሁሉ አንረዳውም:: ህይወታችን በአእምሮ መርምረን የምንጨርሰው አይደለም:: አእምሮን የሚያልፍ ሰላም ልባችንንና አሳባችንን
መጠበቅ ያለበት ህይወታችን ሁሉንም ጠንቅቀን ከምንረዳው በላይ አእምሮን  የሚያልፍ በመሆኑ ነው:: 
አእምሮንም ሁሉ የሚያልፍ የእግዚአብሔር ሰላም ልባችሁንና አሳባችሁን በክርስቶስ ኢየሱስ ይጠብቃል።  ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች  4:7
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa


No comments:

Post a Comment