Popular Posts

Wednesday, June 3, 2020

ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ እምነት ቢኖራችሁ ባትጠራጠሩም፥ . . . ይህን ተራራ እንኳ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ብትሉት ይሆናል፤ የማቴዎስ ወንጌል 21፡21

ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ እምነት ቢኖራችሁ ባትጠራጠሩም፥ . . . ይህን ተራራ እንኳ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ብትሉት ይሆናል፤ የማቴዎስ ወንጌል 21፡21

Sunday, May 31, 2020

የነፍስ ብቻ ሳይሆን የስጋ ፈውስ ያስፈልገናል




ስለዚህ ወደ ዓለም ሲገባ፦ መሥዋዕትንና መባን አልወደድህም ሥጋን ግን አዘጋጀህልኝ፤ ወደ ዕብራውያን 10፡5
በመድር ላይ ለመኖር ለመንቀሳቀስ ለመውጣትና ለመግባት ስጋ ያስፈልጋል፡፡ ኢየሱስ እኛን ከሃጢያት የማዳን ስራ ለመስራት ስጋ አስፈልጎት ነበር፡፡
ኢየሱስ ምንም ሙሉ መንፈሳዊነት ቢኖረው በስጋ ውስጥ ባይኖር ኖሮ ግን የማዳንን አላማ ማስፈፀም አይችልም ነበር፡፡
የነፍስ መዳን በጣም አስፈላጊ ነው፡፡ በምድር ላይ የምንፈፅመው የተለየ አላማ ባይኖረን ኖሮ ነፍሳችን እንደዳነ ወዲያው ወደጌታ እንወሰድ ነበር፡፡
እግዚአብሄር በምድር ላይ እንድንፈፅም የሰጠንን ራእይና አላማ ለመፈፀም ደግሞ በምድር ላይ መኖር አለብን፡፡ በጠንካራ እና በጤነኛ አካል በምድር ላይ ካልኖርን እና ሰይጣን በፈለገው ጊዜ የፈለገውን በሽታ የሚያደርግብን ከሆነ የእግዚአብሄርን ፈቃድ መፈጸም ያቅተናል፡፡
እነሆም፥ ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ የድካም መንፈስ ያደረባት ሴት ነበረች፥ እርስዋም ጐባጣ ነበረች ቀንታም ልትቆም ከቶ አልተቻላትም። ኢየሱስም ባያት ጊዜ ጠራትና። አንቺ ሴት፥ ከድካምሽ ተፈትተሻል አላት፥ እጁንም ጫነባት፤ ያን ጊዜም ቀጥ አለች፥ እግዚአብሔርንም አመሰገነች። ይህችም የአብርሃም ልጅ ሆና ከአሥራ ስምንት ዓመት ጀምሮ ሰይጣን ያሰራት በሰንበት ቀን ከዚህ እስራት ልትፈታ አይገባምን? አለው። የሉቃስ ወንጌል 13፡11-13፣16
እግዚአብሄር በክርስቶስ በኩል የነፍሳችንን መዳኛ መንገድ ብቻ ፈጽሞ ቢሄድ ሰይጣን በስጋችን ላይ የፈለገውን ቢያደርግ የእግዚአብሄርን ፈቃድ በምድር ላይ መፈፀም እንችልም ነበር፡፡
እግዚአብሄር ግን ለነፍሳችን ብቻ ሳይሆን ነፍሳችን ስለሚኖርበት ስለስጋችን ሙሉ ዋጋን ከፍሏል፡፡
መፅሃፍ ቅዱስ በመገረፉ ቁስል እንደተፈወስን የሚናገረው በምድር ላይ የእግዚአብሄርን ፈቃድ ለመፈፀም የነፍሳችን መዳን ብቻ ሳይሆን የስጋችን ብርታት አስፈላጊ ስለሆነ ነው፡፡    
ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ። 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 2፡24
ኢየሱስ በምድር ላይ በነበረበት ጊዜ ስለሰዎች ነፍስ መዳን መስበክ ብቻ ሳይሆን ስለስጋቸውም ፈውስ በትጋት እና በቅናት ይፀልይ የነበረው ስለዚህ ነው፡፡
እግዚአብሔር የናዝሬቱን ኢየሱስን በመንፈስ ቅዱስ በኃይልም ቀባው፥ እርሱም መልካም እያደረገ ለዲያብሎስም የተገዙትን ሁሉ እየፈወሰ ዞረ፥ እግዚአብሔር ከእርሱ ጋር ነበረና፤ የሐዋርያት ሥራ 10፡38
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Tuesday, May 26, 2020

ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 53

ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 53
1፤ የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል?
2፤ በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል። መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም።
3፤ የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም።
4፤ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው።
5፤ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።
6፤ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ።
7፤ ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።
8፤ በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ?
9፤ ከክፉዎችም ጋር መቃብሩን አደረጉ፥ ከባለጠጎችም ጋር በሞቱ ሆኖም ግፍን አላደረገም ነበር፥ በአፉም ተንኮል አልተገንበትም ነበር።
10፤ እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈከደ፤ ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፥ ዕድሜውም ይረዝማል፥ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል።
11፤ ከነፍሱ ድካም ብርሃን ያያል ደስም ይለዋል፤ ጻድቅ ባሪያዬም በእውቀቱ ብዙ ሰዎችን ያጸድቃል፥ ኃጢአታቸውን ይሰከማል።
12፤ ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና፤ እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።