Popular Posts

Friday, March 20, 2020

እግዚአብሔር ተቀብሎታል


በእምነት የደከመውንም ተቀበሉት፥ በአሳቡም ላይ አትፍረዱ። ሁሉን ይበላ ዘንድ እንደ ተፈቀደለት የሚያምን አለ፥ ደካማው ግን አትክልት ይበላል። የሚበላ የማይበላውን አይናቀው የማይበላውም በሚበላው አይፍረድ፥ እግዚአብሔር ተቀብሎታልና። ወደ ሮሜ ሰዎች 14:1-3  
በዚህ ጊዜ በተከሰተው የኮሮና ቫይረስ መከላለያ መንገዶች መካከል በክርስትያኖች መካከል መለያየት ይታያል፡፡ መለያየት በራሱ ክፉ አይደለም፡፡ መለያየትን ተመስርቶ እርስ በእርስ መናናቅ እና መፈራረድ ግን ክፉ ነው፡፡
1.       ተጨማሪ ቫይታሚን የሚወስደው የማይወስደውን አይፍድበት፡፡
2.       ሆስፒታል ሔዶ የሚመረመረው የማይመረመረውን አይናቀው፡፡
3.       የፊት መሸፈኛ ወይም ጓንት የሚያደርገው የፊት መሸፈኛ የማያደርገው ላይ አይፍረድበት
4.       የቤተክርስትያንን ስብሰባ የሚካፈለው የማይካፈለውን አይናቀው፡፡
5.       የሚጨብጠው የማይጨብጠውን አይናቀው፡፡  
6.       ከቤቱ የሚወጣው የማይወጣውን አይፍረድበት፡፡  
አንተም በወንድምህ ላይ ስለ ምን ትፈርዳለህ? ወይስ አንተ ደግሞ ወንድምህን ስለ ምን ትንቃለህ? ሁላችን በክርስቶስ ፍርድ ወንበር ፊት እንቆማለንና። ወደ ሮሜ ሰዎች 14፡10
እንግዲህ ፍጹማን የሆንን ሁላችን ይህን እናስብ፤ በአንዳች ነገርም ልዩ አሳብ ቢኖራችሁ፥ እግዚአብሔር ይህን ደግሞ ይገልጥላችኋል፤ ሆኖም በደረስንበት በዚያ እንመላለስ። ወደ ፊልጵስዩስ ሰዎች 3፡15-16
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ህይወት #የሚፈርድ #የሚያማ #ወንጌል #መውደድ #ፍቅር #የህይወትምስክርነት #መታዘዝ #ማገልገል #መውደድ #እውነት #ትህትና #ትንሳኤ #ህይወት #ወንጌል #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ  #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ 

No comments:

Post a Comment