I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
አቢይ የጥሞና ቃል #ስድስት የእግዚአብሔር መንግሥት ሰላም የእግዚአብሔር መንግሥት ጽድቅና ሰላም በመንፈስ ቅዱስም የሆነ ደስታ ናት እንጂ መብልና መጠጥ አይደለችምና። ወደ ሮሜ ሰዎች 14፡17 እግዚአብሄር ንጉስዋ የሆነ...
-
Understanding God's special purpose in marriage from God's word is crucial. Achieving the purpose of marriage's first establ...
-
በእግዚአብሔር ቅንዓት እቀናላችኋለሁና፥ እንደ ንጽሕት ድንግል እናንተን ለክርስቶስ ላቀርብ ለአንድ ወንድ አጭቻችኋለሁና፤ ነገር ግን እባብ በተንኮሉ ሔዋንን እንዳሳታት፥ አሳባችሁ ተበላሽቶ ...
-
His divine power has given us everything we need for a godly life through our knowledge of him who called us by his own glory and goodne...
-
ሁልጊዜ አዲስ አመት ሲመጣ ደስ ይለናል፡፡ አዲስ አመት ተስፋን ይዞ ይመጣል፡፡ ዘመን ሲለወጥ ያለፈውን እንድንረሳ ያደርገና ብለን ስለምናስብ ለአዲስ አመት እንጓጓለን፡፡ በአዲስ አመት ያለፈውን ደስ የማያሰኘውን ነገር...
-
Believe God exists And without faith, it is impossible to please God because anyone who comes to him must believe that he exists and that ...
-
አቢይ የጥሞና ቃል #ሶስት የሰው ሁለንተናው የነገሩን ሁሉ ፍጻሜ እንስማ፤ ይህ የሰው ሁለንተናው ነውና፤ እግዚአብሔርን ፍራ፥ ትእዛዙንም ጠብቅ። እግዚአብሔር ሥራን ሁሉ የተሰወረውንም ነገር ሁሉ፥ መልካምም ቢሆን ...
-
በመንፈስ ድሆች የሆኑ ብፁዓን ናቸው፥ መንግሥተ ሰማያት የእነርሱ ናትና። ማቴዎስ 5፡3 ልጆች ጣፋጭ ነገር ይወዳሉ፡፡ ስለዚህ ጣፋጭ ነገር ካገኙ መብላታቸውን ብቻ ነው የሚያስቡት፡፡ ጣፋጭ ነገር ብዙ ከበሉ...
-
Live soberly and be vigilant, for the devil, who is not your partner, prowls around like a roaring lion looking for someone to devour. Re...
Sunday, February 28, 2021
Saturday, February 27, 2021
Thursday, February 25, 2021
የበለጠ የተሻለ ከፍ ያለ
ከእርስዋ
በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ። ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ፥ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ። ኦሪት ዘፍጥረት 3፡5-6
እግዚአብሄር
ሰውነ ሲፈጥረው የሚያስፈልገውን ሁሉ አሟልቶ ነው፡፡ ሰው ግን የተሰጠውን ነገር ሳያይ ሲቀር ፣ ሲያናንቅና የተሻለ ነገር ሲፈልግ
ይሳሳታል ከእግዚአብሄርም መንገድ ይወጣል ፡፡ በየትኛውም አለም ያለው ሰው የሚፈተነው በዚህ ነው፡፡
ሰው
እንዴት ሙሉ ተደርጎ እንደተፈጠረ ሳይረዳ ሲቀር የሚፈተነውና የሚወድቀው የተሰጠውን ትቶ የተሻለ ፣ የበለጠ ፣ ከፍ ያለ ነገር ለራሱ
ሲፈልግ ነው፡፡
እግዚአብሄር
ሔዋንን ሙሉ አድጎት ፈጥሯት እያለ የሰይጣንን ንግግር ሰምታ የተሻለ እውቀትንና የበለጠ ሃይልን ፈለገች፡፡ ሔዋን ግን የሚያስፈልጋት
ባላት ሃይል መርካትና ያላትን ሃይል በሚገባ መጠቀም ብቻ ነበር፡፡
አሁን
በየእለት ህይወታችን የምንፈተነው በዚሁ ፈተና ነው፡፡
በተለይ
በክርስቶስ ኢየሱስ አምነን የእግዚአብሄር ልጆች የሆንን ሁላችን እግዚአብሄር አባታችን ሆኗል፡፡ እግዚአብሄር የሚያስፈልገን ሁሉ
በክርስቶስ ሰጥቶናል፡፡ እግዚአብሄር የሰጠንን መረዳት ሳንችን ስንቀር ሙሉ የሆነውን የእግዚአብሄርን አቅርቦት ልናሻሸለው የሚበልጥ
፣ የተሻለና ከፍ ያለ ነገር ለማግኘት ስንሞክር እንሳሳታለን፡፡
አሁን
የሚያስፈልግን ተጨማሪ ገንዘብ ሳይሆን የተሰጠንን ገንዘብ ተረድተን የምንጠቀምበት ጥበብ ነው፡፡
ለእያንዳንዱ
እንደ ዓቅሙ፥ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ሄደ። አምስት መክሊትም የተቀበለው
ሄዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፤ እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ። አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቈፈረና
የጌታውን ገንዘብ ቀበረ። ማቴዎስ 25፡15-18
አሁን
የሚያስፈልገን ተጨማሪ እምነት ሳይሆን ያለንን እምነት ማሰራት ብቻ ነው፡፡
ሐዋርያትም
ጌታን፦ እምነት ጨምርልን አሉት። ጌታም አለ፦ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ሾላ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተተከል
ብትሉት፥ ይታዘዝላችሁ ነበር። ሉቃስ 17፡5-6
አሁን
የሚያስፈልገን ተጨማሪ ዝና ሳይሆን ባለን ዝና ተጠቅመን ሰዎችን ማገልገል ነው፡፡
አሁን
የሚያስፈልገን ተጨማሪ ሃብት ሳይሆን የተሰጠንን ሃብት ለእግዚአብሄር መንግስት ጥቅም እንዴት እንደምናውለው ምሪት መፈለግ ነው፡፡
የሰይጣንም ፈተና ያለንን ርስት እንዳናይ ፣ በሌለን
ላይ እያተኮርን "በምስኪንነት" አስተሳሰብ ህይወታችንን ለምንም የማይጠቅም ሽባ ማድረግ ነው፡፡
ሰይጣን ያለንን እስከናቅን ድረስ ፣ ባለን ነገር
ላይ እርምጃ እሰካልወሰድን እና ሁልጊዜ ለተጨማሪ ፣ ለሚሻልና ለሚበልጥ ሃይል ፣ ስልጣን ፣ ሃብትና ዝና ብንሮጥ ግድ የለውም፡፡
የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ። 2ኛ የጴጥሮስ መልእክት 1፡2-3
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/
ለቪዲዮ መልእክቶች
https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#እረፍት #ቅድሚያ #እምነት
#መደገፍ #ሰንበት
#አስቀድማችሁ #ፅድቁን
#ኢየሱስ #ክርስቶስ
#ጌታ #ቤተክርስትያን
#አማርኛ #ስብከት
#እምነት #መፅሃፍቅዱስ
#መንፈስቅዱስ #ምህረት
#ፌስቡክ #አቢይዋቁማ
#አቢይዋቁማዲንሳ
Tuesday, February 23, 2021
Sunday, February 21, 2021
Life Is Like A Cup of Coffee Inspirational Video Movie
በእምነት ያልሆነ
የሚጠራጠረው ግን ቢበላ በእምነት ስላልሆነ ተኮንኖአል፤ በእምነትም ያልሆነ ሁሉ ኃጢአት ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 14፡23
ሰው
የተፈጠረው በእምነት እንዲኖር ነው፡፡ ሰው በእምነት ካልኖረ የተፈጠረበትን አላማ ይስታል፡፡ ሰው በጥርጥር ከኖረ በህይወቱ ትርጕም
ያለው ነገር ማድረግ ይሳነዋል፡፡
ሰው
የእግዚአብሄርን ስራ ሰራ የሚባለው ሲያምን ነው እንጂ ሃይማኖራዊ ወግና ስርአት ስላደረገ አይደለም፡፡
እንግዲህ፦
የእግዚአብሔርን ሥራ እንድንሠራ ምን እናድርግ? አሉት። ኢየሱስ መልሶ፦ ይህ የእግዚአብሔር ሥራ እርሱ በላከው እንድታምኑ ነው አላቸው።
የዮሐንስ ወንጌል 6፡28-29
የሚጠራጠር
ሰው ከእግዚአብሄር የሚያገኘው በረከት ሙሉ አይሆንም ብቻ ሳይሆን እግዚአብሄርን ስለተጠራጠረ ምንም ነገር አያገኝም፡፡
ነገር
ግን በምንም ሳይጠራጠር በእምነት ይለምን፤ የሚጠራጠር ሰው በነፋስ የተገፋና የተነቃነቀ የባሕርን ማዕበል ይመስላልና። ሁለት አሳብ ላለው በመንገዱም ሁሉ ለሚወላውል ለዚያ ሰው ከጌታ ዘንድ አንዳች እንዲያገኝ አይምሰለው። የያዕቆብ መልእክት 1፡6-8
ሰው
ካመነ በኃላ የጥርጥርን ሃሳብ እንዳያስተናገድ መጠንቀቅ አለበት፡፡ ሰው ካመነ በኃላ በእምነቱ መፅናት አለበት፡፡ ሰው ማመኑ ብቻ
ሳይሆን በእምነት መፅናቱና አለመጠራጠሩ ወሳኝ ነው፡፡ ሰው አምኖ በኃላ በእምነቱ ባይፀናና ቢጠራጠር ወደኃላም ቢያፈገፍግ በረከት
ሊያገኝ አይችልም፡፡
ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ እምነት ቢኖራችሁ ባትጠራጠሩም፥ በበለሲቱ እንደ ሆነባት ብቻ አታደርጉም፤ ነገር ግን ይህን ተራራ እንኳ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ብትሉት ይሆናል፤ የማቴዎስ ወንጌል 21፡21
የሰው
ሃላፊነቱ የእግዚአብሄርን ቃል በቀጣይነት በመስማት እምነቱን መገንባት ብቻ ሳይሆን እምነቱን ሊንድ የሚችለውን የጥርጥርን ኃሳብ
አለማስተናገድ ነው፡፡
ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ በእምነት በረታ እንጂ በአለማመን ምክንያት በእግዚአብሔር ተስፋ ቃል አልተጠራጠረም። ወደ ሮሜ ሰዎች 4፡20-21
ሰው እምነትን ለማግኘት ብቻ ሳይሆን እምነቱን
ለመጠበቅ የእምነት ተጋድሎን መጋደል አለበት፡፡
እምነት እግዚአብሄርን እንደሚያስደስተው ሁሉ እግዚአብሄር
በጥርጥር አይደሰትም፡፡
ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም። እኛ ግን ነፍሳቸውን ሊያድኑ ከሚያምኑቱ ነን እንጂ ወደ ጥፋት ከሚያፈገፍጉ አይደለንም። ወደ ዕብራውያን 10፡38
የሰው
እምነት እግዚአብሄርን እንደሚያስደስተው ሁሉ የሰው ጥርጥር ያሳዝነዋል፡፡
ያለ
እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ ዕብራውያን 11፡6
አቢይ
ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች
https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#እምነት #ማየት #አለማየት
#ቃል #ጥርጥር
#የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት
#እወጃ #ቤተክርስትያን
#አማርኛ #ስብከት
#መዳን #መፅሃፍቅዱስ
#መንፈስቅዱስ #ህይወት
#ፌስቡክ #አቢይዋቁማ
#አቢይዋቁማዲንሳ





