Popular Posts

Saturday, February 27, 2021

Thursday, February 25, 2021

የበለጠ የተሻለ ከፍ ያለ

 

ከእርስዋ በበላችሁ ቀን ዓይኖቻችሁ እንዲከፈቱ እንደ እግዚአብሔርም መልካምንና ክፉን የምታውቁ እንድትሆኑ እግዚአብሔር ስለሚያውቅ ነው እንጂ። ሴቲቱም ዛፉ ለመብላት ያማረ እንደ ሆነ፥ ለዓይንም እንደሚያስጎመጅ፥ ለጥበብም መልካም እንደ ሆነ አየች፤ ከፍሬውም ወሰደችና በላች፤ ለባልዋም ደግሞ ሰጠችው እርሱም ከእርስዋ ጋር በላ። ኦሪት ዘፍጥረት 3፡5-6

እግዚአብሄር ሰውነ ሲፈጥረው የሚያስፈልገውን ሁሉ አሟልቶ ነው፡፡ ሰው ግን የተሰጠውን ነገር ሳያይ ሲቀር ፣ ሲያናንቅና የተሻለ ነገር ሲፈልግ ይሳሳታል ከእግዚአብሄርም መንገድ ይወጣል ፡፡ በየትኛውም አለም ያለው ሰው የሚፈተነው በዚህ ነው፡፡

ሰው እንዴት ሙሉ ተደርጎ እንደተፈጠረ ሳይረዳ ሲቀር የሚፈተነውና የሚወድቀው የተሰጠውን ትቶ የተሻለ ፣ የበለጠ ፣ ከፍ ያለ ነገር ለራሱ ሲፈልግ ነው፡፡

እግዚአብሄር ሔዋንን ሙሉ አድጎት ፈጥሯት እያለ የሰይጣንን ንግግር ሰምታ የተሻለ እውቀትንና የበለጠ ሃይልን ፈለገች፡፡ ሔዋን ግን የሚያስፈልጋት ባላት ሃይል መርካትና ያላትን ሃይል በሚገባ መጠቀም ብቻ ነበር፡፡

አሁን በየእለት ህይወታችን የምንፈተነው በዚሁ ፈተና ነው፡፡

በተለይ በክርስቶስ ኢየሱስ አምነን የእግዚአብሄር ልጆች የሆንን ሁላችን እግዚአብሄር አባታችን ሆኗል፡፡ እግዚአብሄር የሚያስፈልገን ሁሉ በክርስቶስ ሰጥቶናል፡፡ እግዚአብሄር የሰጠንን መረዳት ሳንችን ስንቀር ሙሉ የሆነውን የእግዚአብሄርን አቅርቦት ልናሻሸለው የሚበልጥ ፣ የተሻለና ከፍ ያለ ነገር ለማግኘት ስንሞክር እንሳሳታለን፡፡

አሁን የሚያስፈልግን ተጨማሪ ገንዘብ ሳይሆን የተሰጠንን ገንዘብ ተረድተን የምንጠቀምበት ጥበብ ነው

ለእያንዳንዱ እንደ ዓቅሙ፥ ለአንዱ አምስት መክሊት ለአንዱ ሁለት ለአንዱም አንድ ሰጠና ወደ ሌላ አገር ወዲያው ሄደ። አምስት መክሊትም የተቀበለው ሄዶ ነገደበት ሌላም አምስት አተረፈ፤ እንዲሁም ሁለት የተቀበለው ሌላ ሁለት አተረፈ። አንድ የተቀበለው ግን ሄዶ ምድርን ቈፈረና የጌታውን ገንዘብ ቀበረ። ማቴዎስ 25፡15-18

አሁን የሚያስፈልገን ተጨማሪ እምነት ሳይሆን ያለንን እምነት ማሰራት ብቻ ነው፡፡

ሐዋርያትም ጌታን፦ እምነት ጨምርልን አሉት። ጌታም አለ፦ የሰናፍጭ ቅንጣት የሚያህል እምነት ቢኖራችሁ፥ ይህን ሾላ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተተከል ብትሉት፥ ይታዘዝላችሁ ነበር። ሉቃስ 17፡5-6

አሁን የሚያስፈልገን ተጨማሪ ዝና ሳይሆን ባለን ዝና ተጠቅመን ሰዎችን ማገልገል ነው፡፡

አሁን የሚያስፈልገን ተጨማሪ ሃብት ሳይሆን የተሰጠንን ሃብት ለእግዚአብሄር መንግስት ጥቅም እንዴት እንደምናውለው ምሪት መፈለግ ነው፡፡

የሰይጣንም ፈተና ያለንን ርስት እንዳናይ ፣ በሌለን ላይ እያተኮርን "በምስኪንነት" አስተሳሰብ ህይወታችንን ለምንም የማይጠቅም ሽባ ማድረግ ነው፡፡

ሰይጣን ያለንን እስከናቅን ድረስ ፣ ባለን ነገር ላይ እርምጃ እሰካልወሰድን እና ሁልጊዜ ለተጨማሪ ፣ ለሚሻልና ለሚበልጥ ሃይል ፣ ስልጣን ፣ ሃብትና ዝና ብንሮጥ ግድ የለውም፡፡

የመለኮቱ ኃይል፥ በገዛ ክብሩና በበጎነቱ የጠራንን በማወቅ፥ ለሕይወትና እግዚአብሔርን ለመምሰል የሚሆነውን ነገር ሁሉ ስለ ሰጠን፥ በእግዚአብሔርና በጌታችን በኢየሱስ እውቀት ጸጋና ሰላም ይብዛላችሁ። 2 የጴጥሮስ መልእክት 1፡2-3

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እረፍት #ቅድሚያ #እምነት #መደገፍ #ሰንበት #አስቀድማችሁ #ፅድቁን #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ጌታ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #እምነት #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ምህረት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ


Sunday, February 21, 2021

Life Is Like A Cup of Coffee Inspirational Video Movie

Life is Like a Cup of Coffee
A group of alumni, who were very successful in their careers, decided to get together to visit their old university professor. After they all reunited, the conversation of the alumni soon turned into complaints about work, relationships and life.
Offering his guests coffee, the professor went to the kitchen and returned with a large pot of coffee and an assortment of cups – porcelain, plastic, glass, crystal, some plain looking, some expensive, some exquisite – telling them to help themselves to the coffee.
When all of his old students had a cup of coffee in hand, they sat down together and the professor said: “If you noticed, all the nice looking expensive cups have been taken up, leaving behind the plain and cheap ones. While it is, of course normal for you to want only the best for yourselves, that can also be the source of much of your dissatisfaction, problems and stress.
It’s important to know that the cup itself adds no real quality to the coffee. In most cases it is just chosen because its perceived to be more special or expensive. What all of you really wanted was experience of the coffee, not the cup, but you unconsciously went for the best cups. Some of you tried to get the best cup first or began eyeing each other’s cups to see if yours was nice enough.
Now consider this: Life is a bit like the cup of coffee; the jobs, money possessions and position in society are the cups. They are just tools and structures that contain or hold together the current story of your life, and the type of cup we have does not define, nor change the quality of life we live.
Sometimes, by concentrating only on the cup, we fail to enjoy the coffee. Here is my advice to you – Savour the coffee, not the cups! What you really want is to be happy and The happiest people don’t have the best of everything. They just make the best of everything.
So live simply. Love generously. Care deeply. Speak kindly….and your life will be fully lived.”

በእምነት ያልሆነ

 


የሚጠራጠረው ግን ቢበላ በእምነት ስላልሆነ ተኮንኖአል፤ በእምነትም ያልሆነ ሁሉ ኃጢአት ነው። ወደ ሮሜ ሰዎች 1423

ሰው የተፈጠረው በእምነት እንዲኖር ነው፡፡ ሰው በእምነት ካልኖረ የተፈጠረበትን አላማ ይስታል፡፡ ሰው በጥርጥር ከኖረ በህይወቱ ትርጕም ያለው ነገር  ማድረግ ይሳነዋል፡፡

ሰው የእግዚአብሄርን ስራ ሰራ የሚባለው ሲያምን ነው እንጂ ሃይማኖራዊ ወግና ስርአት ስላደረገ አይደለም፡፡

እንግዲህ፦ የእግዚአብሔርን ሥራ እንድንሠራ ምን እናድርግ? አሉት። ኢየሱስ መልሶ፦ ይህ የእግዚአብሔር ሥራ እርሱ በላከው እንድታምኑ ነው አላቸው። የዮሐንስ ወንጌል 6፡28-29

የሚጠራጠር ሰው ከእግዚአብሄር የሚያገኘው በረከት ሙሉ አይሆንም ብቻ ሳይሆን እግዚአብሄርን ስለተጠራጠረ ምንም ነገር አያገኝም፡፡

ነገር ግን በምንም ሳይጠራጠር በእምነት ይለምን፤ የሚጠራጠር ሰው በነፋስ የተገፋና የተነቃነቀ የባሕርን ማዕበል ይመስላልና። ሁለት አሳብ ላለው በመንገዱም ሁሉ ለሚወላውል ለዚያ ሰው ከጌታ ዘንድ አንዳች እንዲያገኝ አይምሰለው። የያዕቆብ መልእክት 1፡6-8

ሰው ካመነ በኃላ የጥርጥርን ሃሳብ እንዳያስተናገድ መጠንቀቅ አለበት፡፡ ሰው ካመነ በኃላ በእምነቱ መፅናት አለበት፡፡ ሰው ማመኑ ብቻ ሳይሆን በእምነት መፅናቱና አለመጠራጠሩ ወሳኝ ነው፡፡ ሰው አምኖ በኃላ በእምነቱ ባይፀናና ቢጠራጠር ወደኃላም ቢያፈገፍግ በረከት ሊያገኝ አይችልም፡፡

ኢየሱስም መልሶ፦ እውነት እላችኋለሁ፥ እምነት ቢኖራችሁ ባትጠራጠሩም፥ በበለሲቱ እንደ ሆነባት ብቻ አታደርጉም፤ ነገር ግን ይህን ተራራ እንኳ፦ ተነቅለህ ወደ ባሕር ተወርወር ብትሉት ይሆናል፤ የማቴዎስ ወንጌል 21፡21

የሰው ሃላፊነቱ የእግዚአብሄርን ቃል በቀጣይነት በመስማት እምነቱን መገንባት ብቻ ሳይሆን እምነቱን ሊንድ የሚችለውን የጥርጥርን ኃሳብ አለማስተናገድ ነው፡፡  

ለእግዚአብሔርም ክብር እየሰጠ፥ የሰጠውንም ተስፋ ደግሞ ሊፈጽም እንዲችል አጥብቆ እየተረዳ፥ በእምነት በረታ እንጂ በአለማመን ምክንያት በእግዚአብሔር ተስፋ ቃል አልተጠራጠረም። ወደ ሮሜ ሰዎች 4፡20-21

ሰው እምነትን ለማግኘት ብቻ ሳይሆን እምነቱን ለመጠበቅ የእምነት ተጋድሎን መጋደል አለበት፡፡

እምነት እግዚአብሄርን እንደሚያስደስተው ሁሉ እግዚአብሄር በጥርጥር አይደሰትም፡፡  

ጻድቅ ግን በእምነት ይኖራል ወደ ኋላም ቢያፈገፍግ፥ ነፍሴ በእርሱ ደስ አይላትም። እኛ ግን ነፍሳቸውን ሊያድኑ ከሚያምኑቱ ነን እንጂ ወደ ጥፋት ከሚያፈገፍጉ አይደለንም። ወደ ዕብራውያን 10፡38

የሰው እምነት እግዚአብሄርን እንደሚያስደስተው ሁሉ የሰው ጥርጥር ያሳዝነዋል፡፡

ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ ዕብራውያን 11፡6

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#እምነት #ማየት #አለማየት #ቃል #ጥርጥር #የእግዚአብሄርሃይል #መንፈስቅዱስ #ቃሉንመስማት #እወጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ