Popular Posts

Thursday, August 22, 2024

ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር ክፍል 5

 


እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃምምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ። 1 ወደጢሞቴዎስ 21-2

መፅሃፍ ቅዱስ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉእንዲደረጉ እያስተማረ ይህንን ምክር እስከማንቀበል ድረስ የምንቃወም ከሆንን ለስጋችን አርነት እየሰጠንእንደሆነ ግልጽ ነው፡፡ 

ምክኒያቱም ስልጣን ሁሉ ከእግዚአብሄር ነው፡፡ 

ነፍስ ሁሉ በበላይ ላሉት ባለ ሥልጣኖች ይገዛ። ከእግዚአብሔር ካልተገኘ በቀር ሥልጣን የለምና፤ ያሉትም ባለሥልጣኖች በእግዚአብሔር የተሾሙ ናቸው። ወደ ሮሜ ሰዎች 131

ሰይጣን እግዚአብሄርን አታልሎት የተሾመ ባለስልጣን የለም፡፡  ስልጣን የእግዚአብሄር ስርአት አካል ነው፡፡የማንኛውም ስልጣን አላማ ደግሞ መልካም አስተዳር ነው፡፡ የእግዚአብሄር ስርአት ደጋፊዎች ነን፡፡ እንደክርስትያን ለዚህ የእግዚአብሄር ስርአት ግብ መምታት ልመናና ፀሎት ምልጃም ምስጋናም ማቅረብ ይገባናል፡፡ 

ባለስልጣንን በቅድሚያ የምናየው በእግዚአብሄር ስርአት ነው፡፡ ባለስልጣንን የምናየው በመልካነቱ ወይምበክፉነቱ ሳይሆን በእግዚአብሄር ስርአት አስፈፃሚነቱ ነው፡፡ 

ሃላፊነታችንን ሳንወጣ ብናጉረመርም ምንም የሚመጣ ውጤት አይኖርም፡፡ ነገር ግን ፀጥ እና ዝግ ብለንለመኖር ልመናና ጸሎት እና ምልጃም ምስጋናም ማቅረብ ክርስቲያናዊ ግዴታችን ነው፡፡ 

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ  Abiy Wakuma Dinsa

 #ጸጥ #ዝግ #እግዚአብሔርንመምሰል #ፀሎት #ኢየሱስ #ጌታ #ምልጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት#መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ምስጋና #እምነት #ነገስታት #መኳንንት #አማርኛ #ሰላም #ደስታ #አቢይ#አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ኢትዮጲያ #ፖለቲካ #መንግስት


Monday, August 19, 2024

ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር ክፍል 4

 

ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር ክፍል 4

እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃምምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ። 1 ወደጢሞቴዎስ 21-2

መጽሃፍ ቅዱስ በሚያዘው መሰረት ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለመኳንንትም ሁሉ ማድረጋችን እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖርያስችለናል፡፡ 

ነገር ግን እንደ ክርስትያን ከልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ውጭ የሆነ እና እነዚህን ያላካተተ ማንኛውምመፍትሄ ፍሬያማ ሊሆን አይችልም፡፡ 

ክርስትያን ስለፍትህ መጮህ ይገባዋል፡፡ ነገር ግን ከልመናና ጸሎት ከምልጃና ምስጋና ውጭ የሆነ ባዶ ተቃውሞየታለመለትን አላማ ግብ ሊመታ አይችልም፡፡ ከልመናና ጸሎት ከምልጃና ምስጋና ያላስቀደመ ማንኛውም ነገርመፍትሔ ሊሆን አይችልም። 

ስለነገስታት እና መኳንንት ከሚደረግ ልመናና ጸሎት ምልጃና ምስጋና የጎደለው ተቃውሞ ለስጋዊ ምኞት አርነትንመስጠት ብቻ ነው፡፡ 

ነገስታትን መኳንንትን ሰዎችን ሁሉ በልመና እና በጸሎት በምልጃ እና በምስጋና እንድናገለግል ተጠርተናል፡፡የማንወደውን ሰው በጸሎት ልናገለግለው አንችልም፡፡ ልንፀልይለት እስከማንችን ድረስ የምንጠላውን ሰውበፍፁም ልናገለግለው በፀሎት ልንደግፈው አንችልም፡፡ ልመና እና ጸሎት ምልጃ እና ምስጋና እንድናደርግከሚመክረን ከእግዚአብሔር ጋር በመወገን የእግዚአብሔርን ስርአት እንደግፍ። 

ስለዚህ ትሁት ሆነን ለስጋችን አርነት ሳንሰጥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትናስለ መኳንንትም ሁሉ እናድርግ፡፡ 

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ  Abiy Wakuma Dinsa

 #ጸጥ #ዝግ #እግዚአብሔርንመምሰል #ፀሎት #ኢየሱስ #ጌታ #ምልጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት#መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ምስጋና #እምነት #ነገስታት #መኳንንት #አማርኛ #ሰላም #ደስታ #አቢይ#አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ኢትዮጲያ #ፖለቲካ #መንግስት

Saturday, August 17, 2024

 

ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር ክፍል 3

እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ። 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2፡1-2

መፅሃፍ ቅዱስ ስለሰዎች በተለይ ስለነገስታት መፀለያችን ጸጥ እና ዝግ ብለን እንድንኖር እንደሚያስችለን መፅሃፍ ቅዱስ አጥብቆ ይመክረናል፡፡  

ክርስትያን ባለው መንግስታዊ አስተዳደር ደስተኛ ሊሆንም ይችላል ላይሆንም ይችላል፡፡ አንዳንድ ጊዜ በነገስታቱ እና በመኳንንቱ ላይ ቅሬታ ሊኖረው ይችላል፡፡ በነገስታቱ እና በመኳንንቱ ላይ ቅሬታ አለው ማለት ግን ልመናና ጸሎት ምልጃና ምስጋና እንዳያቀርብ ፈቃድ ይሰጠዋል ማለት ግን አይደለም፡፡ 

በነገስታቱ እና በመኳንንቱ የሚወሰነውን ውሳኔ ይደግፍም ይቃወምም ክርስትያን ከመፀለይ ውጭ ተበላሽቷል የሚላቸውን ነገሮችን ለማስተካከል የሚችልበት ሌላ ምንም አማራጭ አይኖረውም፡፡ 

እንዲያውም የተበላሹትን ነገሮች የምናስተካክልበትና በዚያም ጸጥ እና ዝግ ብለን መኖር የምንችልበት መንገድ  ልመናና ጸሎት ምልጃና ምስጋና አብዝተን ማቅረባችን ብቻ ነው፡፡ 

ክርስትያን እንደአገር ዜጋ በፖለቲካ ወይም በአገር አስተዳደር ጉዳዮች መሳተፍ ይኖርበታል፡፡ ክርስትያን የተበላሹ ነገሮች እንዲስተካከሉ የመናገር እና የመሞገት ሃላፊነት እንዳለበት አሌ የማይባል ሃቅ ነው፡፡  

ክርስትያን ተቃዋሚ ፓርቲ ውስጥ መሳተፍ እና አማራጭ የፖለቲካ ፖሊሲዎችን ማራመድ ይችላል፡፡ ነገር ግን ተቃዋሚነቱ የእግዚአብሄር ስርአት ወገን ከመሆን ሊያግደው በፍፁም አይገባም፡፡ ከገዢው ፓርቲ የተለየ አቋም መያዙ ለነገስታቱ እና ለመኳንንቱ ለሰዎች ሁሉ እንዳይፀልይ ሊያግደው አይገባም፡፡ ተቃዋሚነቱ ለነገስታቱ እና ለመኳንንቱ  እስካለመፀለይ ድረስ ካደረሰው የእግዚአብሄርን ስርአት ይቃወማል፡፡ ምንም አይነት የፖለቲካ አቋሙ የእግዚአብሄርን ስርአት እንዲቃወም ማለትም ስለነገስታ እና ስለመኳንንቱ እንዳይፀልይ ሊያደርገው አይገባም፡፡  

ከማንኛውም የፖለቲካ አመለካታችን በላይ እንደ ክርስትያን ስለ ነገስታ እና መኳንንት እንዲሁም ስለ ሰዎች ሁሉ ልመናና ጸሎት ምልጃና ምስጋና ልናቀርብ ይገባናል፡፡  

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ  Abiy Wakuma Dinsa

 #ጸጥ #ዝግ #እግዚአብሔርንመምሰል #ፀሎት #ኢየሱስ #ጌታ #ምልጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ምስጋና #እምነት #ነገስታት #መኳንንት #አማርኛ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ኢትዮጲያ #ፖለቲካ #መንግስት

Thursday, August 15, 2024

ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር ክፍል 2

 

እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ። 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2፡1-2

በማንኛውም የህይወታችን ክፍል  ጸጥና ዝግ ብሎ የመኖሩ ሚስጥር መፅሃፍ ቅዱስ አስቀድመን እንድናደርግ የመከረውን ነገር መተግበሩ ላይ ነው፡፡ 

ጸጥ እና ዝግ ብለን የመኖሩ ሃላፊነት በእኛ ጫንቃ ላይ እንደወደቅ ማወቃችን እግዚአብሔር ከእኛ የሚጠብቀውን ነገር በማድረግ ፍሬያማ እንድንሆን ያበረታታናል፡፡  

አስቀድመን እንድናደርግ የተመከርነው ነገር ልመናና ጸሎት እንዲሁም ምልጃም ምስጋና ነው፡፡ ልመናና ጸሎት ማድረግ እንዲሁም ምልጃና ምስጋና ማቅረብ የክርስትና ቀዳሚው ሃላፊነታችን ነው፡፡ 

በሰዎች ህይወት ውስጥ የምናያቸው ጉድለቶች መፍትሄው ያለው ከእግዚአብሔር ዘንድ ነው፡፡ አይናችንን አንስተን መፍትሄ ወዳለበት ወደ ሰማይ ለለውጥ መጮህ አለብን፡፡ 

ወደ እኔ ጩኽ፥ እኔም እመልስልሃለሁ፤ አንተም የማታውቀውን ታላቅና ኃይለኛ ነገርን አሳይሃለሁ። ትንቢተ ኤርምያስ 33፡3

ብዙ ጊዜ ግን መፍትሄን የምንፈልገው መፍትሄ ከሌላቸው ቦታዎች ነው፡፡ መፍትሄ የሌላቸው ለሚመስሉ  ነገሮች ሁሉ መፍትሄ የሚመጣው ከእግዚአብሔር ዘንድ ብቻ ነው፡፡ 

እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ። 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2፡1-2

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ  Abiy Wakuma Dinsa 

 #ጸጥ #ዝግ #እግዚአብሔርንመምሰል #ፀሎት #ኢየሱስ #ጌታ #ምልጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ምስጋና #እምነት #ነገስታት #መኳንንት #አማርኛ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ኢትዮጲያ #ፖለቲካ #መንግስት

Wednesday, August 14, 2024

ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር ክፍል 1

እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ። 1 ወደ ጢሞቴዎስ 21-2

መቼም ጸጥና ዝግ ብሎ መኖር የማይፈልግ ማንም ሰው የለም፡፡ በዚህ የመፅሃፍ ቅዱስ ክፍል ውስጥ ሐዋርያው ጳውሎስ ጸጥና ዝግ ብሎ ለመኖር ክርስትያን ምን ማድረግ እንደሚገባው ይመክራል፡፡ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ የሚለው አባባሉ እንደ ክርስትያን እጅግ በጣም ከፍተኛ አፅንኦት መስጠት የሚገባን ሃላፊነት ያመለክታል፡፡

በዚህ ክፍል ውስጥ የሚመክረን ነገር ከሌሎች ሃላፊነታችን ሁሉ ሁሉ አስቀድመን ልዩ ቅድሚያ በመስጠት ሃላፊነታችንን መወጣት ያለብን ነገር እንደሆነ ስናስብ ምክሩን በተጠንቀቅ እንድንሰማው ያስገድደናል፡፡

ምንም ሌሎች ነገሮችን ብናደርግ እንኳን አስቀድመን ማድረግ ያለብንን ይህንን ነገር አለማድረግ ጸጥና ዝግ ብለን የመኖር አላማችንን እንደሚያስተጓጉለው ግልፅ ነው፡፡ ሌሎች አስፈላጊ ነገሮችን ሁሉ ማድረጋችን  አስቀድመን ማድረግ ያለብንን ይህን ነገር በፍፁም ሊተካው እንደማይችን እንመለከታለን፡፡ ስለዚህ አስቀድመን ማድረግ ያለብንን ነገር ካላደረግን ሌሎች ነገሮችን ማድርጋችን ብቻ ውጤት እንደማይኖረው በግልፅ እናያለን፡፡

በሚቀጥለው በክፍል ሁለት ፅሁፍ ጸጥ እና ዝግ ብለን እንድንኖር አስቀድመን ምን ማድረግ እንዳለብን እናያለን፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ  Abiy Wakuma Dinsa  

 #ጸጥ #ዝግ #እግዚአብሔርንመምሰል #ፀሎት #ኢየሱስ #ጌታ #ምልጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ምስጋና #እምነት #ነገስታት #መኳንንት #አማርኛ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ኢትዮጲያ #ፖለቲካ #መንግስት


 

Sunday, August 11, 2024

የመንግስቱ ኢኮኖሚ

ኢኮኖሚ ምጣኔ ሀብት ነው፡፡ ሀብት ውስን ነው። የምጣኔ ሀብትጥናት ውስን የሆነውን 


ሀብት መጥኖ ስለመጠቀም ያስተምራል፡፡ውስን የሆነውን ሀብት ቅድሚያ ለሚሰጠው ነገር በሚገባካልተጠቀምንበት አላግባብ ይባክናል።  የእግዚአብሔር መንግስትምጣኔ ሀብት የሚሰራው በመልካም አስተዳደር ነው። በህይወታችንውስጥ ያለው ፀጋ  ክህሎት  ጊዜ እና ጉልበት ሁሉ ለታቀደለትለእግዚአብሔር ፈቃድ ብቻ ካልተጠቀንበት ይባክናል። እግዚአብሔርየሰጠን ማንኛውም ስጦታ ውስን እና ከእግዚአብሔር ፈቃድ ውጭለሆነ ነገር የሚበቃ አይደለም። የእግዚአብሔር አቅርቦት ለፈቃዱበትክክል የሚበቃ እንጂ የሚያንስም የሚጎድልም አይደለም።  እግዚአብሔር የሰጠንን አቅርቦታ ፈቃዱ ባልሆነ ነገር ላይከተጠቀምንበት እና አላግባብ ካባከንነው የእግዚአብሔርን ፈቃድመፈፀም ያቅተናል። ለፈቃዱ የማንጠቀምበት ሁሉ ለታለመለትአላማ ስላልዋለ የአመፃ ገንዘብ ይባላል። እኔም እላችኋለሁ፥ የዓመፃገንዘብ ሲያልቅ በዘላለም ቤቶች እንዲቀበሉአችሁ፥ በእርሱወዳጆችን ለራሳችሁ አድርጉ። የሉቃስ ወንጌል 16:9

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ 

Abiy Wakuma Dinsa

 #ራዕይ #ምሪት #የእግዚአብሄርአጀንዳ #የእግዚአብሄርፈቃድ#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን#መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #አማርኛ #ሰላም#ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር#ኢትዮጲያ #ትግስት #መሪ


Saturday, August 10, 2024

በጣቴ እንኳን ልነካው አልወድም



እግዚአብሔ ሔር የአላማ አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሔር የሚወደው እና የማይወደው የተለየ ነገር አለ፡፡ እግዚአብሔር ለህይወታችን የሚፈልገው እና የማይፈልገው ነገር አለ፡፡ እግዚአብሔር ለህይወታችን ያቀደው የተለየ እቅድ አለ፡፡

በህይወቴ የእግዚአብሔር ፈቃድ ምን ያህል ወሳኝ እንደሆነ ተረድቻለው፡፡ ካለ እግዚአብሔር እቅድ ምንም ነኝ ፣ ምንም የለኝም ፣ ምንም ላደርግ አልችልም፡፡

እግዚአብሔርን፦ አንተ ጌታዬ ነህ አልሁ፤ ከአንተ በቀር በጎነት የለኝም። መዝሙረ ዳዊት 16፡2

በህይወቴ ያለው ማንኛውም አቅርቦት ከእግዚአብሔር ፈቃድ ጋር ብቻ የተያያዘ ነው፡፡ እግዚአብሔር በህይወቴ የሰጠኝ ጊዜ ፣ ችሎታ ፣ ስጦታ ፣ ክህሎት ፣ ፀጋ እና ጥበብ ሁሉ ለፈቃዱ ማስፈፀሚያ እንዲውል ብቻ ነው፡፡

ስለዚህ ያለኝን ማንኛውም ስጦታ እና ክህሎት ለእግዚአብሔር  ፈቃድ ካልተጠቀምኩበት አባክነዋለው እንጂ ለምንም አይጠቅምም፡፡

ከፈቃዱ ውጭ የምጠቀምበት ምንም ትርፍ ስጦታ እና አቅርቦት የለም፡፡ እግዚአብሔር የሰጠኝ ስጦታ ለፈቃዱ አያንስም፡፡ እንዲሁም ደግሞ እግዚአብሔር ለፈቃዱ ከምጠቀምበት በላይ ትርፍ ነገር አይሰጠኝም፡፡ ለእግዚአብሔርም ፈቃድ እንዲሁም ፈቃዱ ላልሆነም ነገር የሚበቃ ምንም ትርፍ እቅርቦት የለኝም፡፡  

የእግዚአብሔርን ፈቃድ ለማስፈፀም የተሰጠኝን ስጦታ ሁሉ በእግዚአብሔር ፈቃድ ላይ ብቻ ለማዋል እተጋለሁ፡፡ የእግዚአብሔ ፈቃድ እንዳለበት ባረጋገጥኩት ነገር ላይ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳልል በሙሉ ልቤ እረባረባለሁ፡፡

በተቃራኒው ደግሞ የእግዚአብሔ ፈቃድ እንዳለበት አጥብቄ ባልተረዳሁበት ነገር ላይ ጊዜዬን ጉልበቴን እውቀቴን አላባክንም፡፡

የእግዚአብሔር ፈቃድ የሌለበትን ነገር በጣቴ እንኳን ልነካው አልወድም፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ

Abiy Wakuma Dinsa

 #ራዕይ #ምሪት #የእግዚአብሄርአጀንዳ #የእግዚአብሄርፈቃድ #ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #አማርኛ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ኢትዮጲያ #ትግስት #መሪ