Popular Posts

Wednesday, September 1, 2021

የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 17

 

ወዳጅ ሆይ፥ ነፍስህ እንደሚከናወን፥ በነገር ሁሉ እንዲከናወንልህና ጤና እንዲኖርህ እጸልያለሁ። 3 ዮሐንስ 12

ሰው ጤናውን ጨምሮ በነገር ሁሉ እንዲከናወንለት እግዚአብሄር ይፈልጋል፡፡

ሰው በምድር ላይ ለመኖር ለመስራትና ለመንቀሳቀስ ጤና ያስፈልገዋል፡፡ እግዚአብሄርን ሰውን ከመፍጠሩ በፊት ያበጀው በምድር ላይ የሚኖርበትን ስጋውን ነው፡፡ ሰው ነፍሱ ተከናውኖ ነገር ግን በስጋው ደካማና የማይችል ከሆነ ክንውኑ ሙሉ ሊሆን አይችልም፡፡ ሰው ነፍሱ ከጠላት ዲያቢሎስ ጥቃት አምልጣ ስጋው ግን የሰይጣን በሽታ መጫወቻ ከሆነ በምድር ላይ ያለውን ተልእኮ በሙላት መፈፀም አይችልም፡፡ 

እውነት ነው እግዚአብሄር ከነፍስ ፈውስ ይልቅ ለስጋ ፈውስ ቅድሚያ አይሰጥም፡፡ ሰው ደግሞ ነፍሱ እንድትድን ስጋው ተፈውሶ የመዳኛ እድልን ማግኘት አለበት፡፡ ስለዚህ ሰው ተፈውሶ ረጅም እድሜ እንዲኖርና የመዳኛን እድልን እንዲያገኝ እግዚአብሄር እርሱን የሚከተል ሰው ብቻ ሳይሆን ያልዳነንም ሰው ስጋ ይፈውሳል፡፡

ኢየሱስ ሰውን ይፈውስና ደግመህ ሃጢያትን አታድርግ ብሎ ማዘዙ የሚያሳየው በሃጢያት ውስጥ ያለ ሰው እንኳን እንዲፈወስና ለእግዚአብሄር ለመኖር እንዲወስን እግዚአብሄር ሌላ እድል መስጠትን እንደሚወድ ነው፡፡ 

ኢየሱስ፦ ተነሣና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ አለው። ወዲያውም ሰውዬው ዳነ አልጋውንም ተሸክሞ ሄደ። ከዚህ በኋላ ኢየሱስ በመቅደስ አገኘውና፦ እነሆ፥ ድነሃል፤ ከዚህ የሚብስ እንዳይደርስብህ ወደ ፊት ኃጢአት አትሥራ አለው። ሰውዬው ሄዶ ያዳነው ኢየሱስ እንደ ሆነ ለአይሁድ ነገረ። ዮሃንስ 5 8-914-15

እግዚአብሄር በመለኮታዊ ፈውስ ብቻ ሳይሆን ለህክምና ባለሙያዎች በሰጠው ተፈጥሮአዊ ጥበብ አማካኝነት በህክምና የሰዎችን ጤና ይመልሳል፡፡ ሰው በምድር ኖሮ እርሱን ለመከተልና ለማገልገል እንዲችል እግዚአብሄር ሰውን በመለኮታዊውም መንገድ ይሁን በተፈጥሮአዊው መንገድ ተጠቅሞ ሰዎችን ከበሽታቸው ያድናል፡፡   

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ


No comments:

Post a Comment