Popular Posts

Friday, September 3, 2021

የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 19

 

የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 19

ምንም እንኳን የሰው ልጅ የነፍስ ፈውስና የስጋ ፈውስ ተሰርቶ ያለቀ ቢሆንም ማንኛውንም መንፈሳዊን ነገርን ለመቀበል እምነት ይጠይቃል፡፡

ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ እግዚአብሔር እንዳለ ለሚፈልጉትም ዋጋ እንዲሰጥ ያምን ዘንድ ያስፈልገዋልና። ዕብራዊያን 11፡6

ፈውስን በህይወታችን ለመቀበል እምነት ይጠይቀናል፡፡

በመንፈሳዊ ልውውጥ ወይም ግብይት እምነት ወሳኝ ነው፡፡

በምድራዊ ግብይት የምንፈልገውን እቃ ለመግዛት ገንዘብን እንደሚጠይቅ ሁሉ በመንፈሳዊ አለም የእኛ የሆነውን በነፃ የተሰጠንን ለመቀበል እምነት ይጠይቃል፡፡

በምድራዊው አለም የአንድ ነገር ዋጋ የሚለካው በገንዘብ እንደሆነ ሁሉ በመንፈሳዊ አለም የአንድ ነገር ዋጋ የሚለካውና የሚወሰነው በእምነት ነው፡፡  

በምድራዊው አለም ገበያ ገንዘብ መግባቢያ ቋንቋ እንደሆነ ሁሉ በመንፈሳ አለም መግባቢያ ቋንቋው እምነት ነው፡፡

ሃዋሪያው ጳውሎስ በምድር ላይ ባገለገለበት ጊዜ የእግዚአብሄርን ቃል ያስተምር ነበር፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ሲናገር ይሰማ ስለነበረው ሰው የእግዚአብሄር ቃል ሲናገር "ይድን ዘንድ እምነት እንዳለው ባየ ጊዜምነት እንዳለው ባየ ጊዜ" ይላል፡፡

ይህም ሰው ጳውሎስ ሲናገር ይሰማ ነበር፤ እርሱም ትኵር ብሎ ተመለከተውና ይድን ዘንድ እምነት እንዳለው ባየ ጊዜ፥ በታላቅ ድምፅ፦ ቀጥ ብለህ በእግርህ ቁም አለው። ብድግ ብሎም ተንሥቶ ይመላለስ ነበር። ሐዋሪያት 14፡9-10

ሃዋሪያው ጳውሎስ የእግዚአብሄርን ቃል ይሰብካል፡፡ ለፈውስ እምነት ስለሚጠይቅ ቃሉን ሰምተው ያመኑ ሰዎች ይፈወሱ ነበር፡፡

በኢየሱስ አገልግሎት ሰዎች ሊሰሙትና ሊፈወሱ ይመጡ ነበር፡፡

ደግሞም ሊሰሙትና ከደዌአቸው ሊፈወሱ ከይሁዳ ሁሉ ከኢየሩሳሌምም ከጢሮስና ከሲዶና ባሕር ዳርም የመጡ ብዙ ሰዎች ነበሩ፤ ሉቃስ 6፡17

ኢየሱስ ሰዎች በኢየሱስ አገልግሎት ከተፈወሱ በኋላ እምነትሽ አድኖሃል የሚለው ስለዚህ ነው፡፡

እርሱንም፦ ተነሣና ሂድ፤ እምነትህ አድኖሃል አለው። ሉቃስ 17፡19

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ


No comments:

Post a Comment