Popular Posts

Monday, September 13, 2021

የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 20

 


የእግዚአብሄርን ፈውስ በህይወታችን ስንፈልግ በእምነት መቅረብ ይኖርብናል፡፡

በእምነት መቅረብ ማለት ደግሞ በአንድ ልብ መቅረብ ማለት ነው፡፡

ወደእግዚአብሄር ስንቀርብ በእምነት መቅረብ ይጠበቅብናል፡፡ ወደ እግዚአብሄር ስንቀርብ በጥርጥር መወላወል መቅረብ የለብንም፡፡

ነገር ግን በምንም ሳይጠራጠር በእምነት ይለምን፤ የሚጠራጠር ሰው በነፋስ የተገፋና የተነቃነቀ የባሕርን ማዕበል ይመስላልና። ሁለት አሳብ ላለው በመንገዱም ሁሉ ለሚወላውል ለዚያ ሰው ከጌታ ዘንድ አንዳች እንዲያገኝ አይምሰለው። ያዕቆብ 1፡6-8

እግዚአብሄርንና የእግዚአብሄርን ነገር በፍፁም ልባችን መፈለግ አለብን፡፡

በሙሉ ልብ ፈውስን የመፈለግ ምሳሌ የምትሆነን ሴት በመፅሃፍ ቅዱስ ውስጥ ምሳሌዋን እናገኛለን፡፡

እነሆም፥ ከነናዊት ሴት ከዚያ አገር ወጥታ፦ ጌታ ሆይ፥ የዳዊት ልጅ፥ ማረኝ፤ ልጄን ጋኔን ክፉኛ ይዞአታል ብላ ጮኸች። እርሱ ግን አንዳች አልመለሰላትም። ደቀ መዛሙርቱም ቀርበው፦ በኋላችን ትጮኻለችና አሰናብታት እያሉ ለመኑት። እርሱም መልሶ፦ ከእስራኤል ቤት ለጠፉት በጎች በቀር አልተላክሁም አለ። እርስዋ ግን መጥታ፦ ጌታ ሆይ፥ እርዳኝ እያለች ሰገደችለት። እርሱ ግን መልሶ፦ የልጆችን እንጀራ ይዞ ለቡችሎች መጣል አይገባም አለ። እርስዋም፦ አዎን ጌታ ሆይ፤ ቡችሎችም እኮ ከጌቶቻቸው ማዕድ የወደቀውን ፍርፋሪ ይበላሉ አለች። በዚያን ጊዜ ኢየሱስ መልሶ፦ አንቺ ሴት፥ እምነትሽ ታላቅ ነው፤ እንደወደድሽ ይሁንልሽ አላት። ልጅዋም ከዚያች ሰዓት ጀምሮ ዳነች። ማቴዎስ 15፡22-28

ይህች ሴት የእግዚአብሄርን ፈውስ ባጣ ቆየኝ አላደረገችውም፡፡ ይህች ሴት አንተ ካልፈወስክልኝ ማንም ሊፈውስልኝ አይችልም ብላ በፍፀም ልብዋ በፅናት ፈውስን ፈለገች፡፡

ኢየሱስ እምነትዋን ታላቅ እንደሆነ መሰከረላት፡፡

እምነትዋም ፈውስን ከእግዚአብሄር እንድትቀበል አደረጋት፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment