Popular Posts

Thursday, September 2, 2021

የአርባ ቀን የፈውስ ትምህርት ጉዞ ቁጥር 18

 


የእግዚአብሄር የመጀመሪያ ፈቃዱ ሰው በጤንነት እንዲኖር ነበር፡፡ ከዚያም በኋላ ሰው በማንኛውም ምክኒያት ጤንነቱን ቢያጣ እግዚአብሄር ሊፈውሰው ይፈልጋል፡፡

ሰው በስጋ የሚፈወሰው እግዚአብሄር በክርስቶስ የተገረፈለትን ሲመለከት እና ሲረዳ ብቻ ነው፡፡

ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ። 1ኛ የጴጥሮስ መልእክት 2፡24

ሰው ካልተፈወሰ ያልተፈወሰው እግዚአብሄር ስላልፈቀደ ሳይሆን ሰው ለጤናው የእግዚአብሄርን ፈቃድ ፈልጎ ስላላገኘ ነው፡፡ ሰው ለመፈወስ ስለፈውሱ የእግዚአብሄርን ቃል ፈልጎ ማግኘት እና መረዳት አለበት፡፡ ሰው ስለስጋው ፈውስ የእግዚአብሄርን ሃሳብ መረዳት ሲጀምር ፈውሱ ይበቅላል፡፡

እንግዲያስ እምነት ከመስማት ነው መስማትም በእግዚአብሔር ቃል ነው። ሮሜ 10፡17

ሰው ከነፍስ የሃጢያት ህመም የማይፈወሰው እግዚአብሄር ፈውሱን ስላልፈቀደ አይደለም፡፡

ሰው ለነፍሱ መድሃኒት ክርስቶስ በመስቀል ላይ ያደረገለትን ነገር ሲመለከት ከነፍስ የሃጢያት ህመም ይፈወሳል፡፡ እንዲሁም ሰው ከስጋ በሽታ የማይፈወሰው እግዚአብሄር ስላልፈቀደ አይደለም፡፡ ሰው እግዚአብሄር በክርስቶስ የሰራለትን ነገር ሲመለከት ይፈወሳል፡፡

ሰው በነፍሱ ከሃጢያት ለመዳን የእግዚአብሄር ፈቃድ ከሆነ ያድነኛል ብሎ ዝም ብሎ መቀመጥ የለበትም፡፡ ሰው በነፍስ ለመዳን እግዚአብሄርን መፈለግና የእግዚአብሄር ቃል ስለነፍሱ የሚለውን ነገር መቀበል ይገባዋል፡፡

እንዲሁም ሰው እግዚአብሄር ከወደደ ያድነኛል ብሎ ስለስጋ ፈውሱ ምንም ነገር ሳያደርግ እጁን አጣጥፎ መቀመጥ የለበትም፡፡ እግዚአብሄር የሰውን መፈወስ ይፈልጋል፡፡

ብዙን ጊዜ እኛ ራሳችንን ዝቅ አድርገን እንደምንመለከተው እግዚአብሄር አያየንም፡፡ እግዚአብሄር ቃሉን እንድንፈልግና እንድናምን ይጠብቅብናል፡፡ እግዚአብሄር ሰው በህይወቱ ስለሚፈልገው ነገር እርሱን እንዲፈልገውና በቃሉ የተናገረውን እንዲያምነው ይጠብቃል፡፡

ፈውሳችንን በእምነት እንድንወስድ እግዚአብሄር ይጠብቅብናል፡፡

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/

ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos

#ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #ፈውስ #ስጋ #ጤንነት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #እምነት #ተስፋ #አሁን #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

No comments:

Post a Comment