Popular Posts

Saturday, October 8, 2016

ልባችሁን በመንገዳችሁ ላይ አድርጉ

ህይወት ጥንቃቄን የሚጠይቅ የስራ ሃላፊነት ነው፡፡ ይህን ሃላፊነት በሚገባ ልንወጣው እንችላለን ወይም ደግሞ ይህን ሃላፊነት በሚገባ ላንወጣው እንችላለን፡፡ ማቴዎስ 25፡14-23

ልቡን በመንገዱ ላይ ሳያደርግ ሳያስብ ፣ ሳያስተውል በዘፈቀደ የሚኖር ሰው አለ፡፡ ይህ የህይወት እውነታ ነው፡፡ አንዳንዱ እግዚአብሄርን ሲያስደስት ይኖራል አንዳንዱ ሲያሳዝነው ዘመኑ ያልፋል፡፡ እግዚአብሄር አባቱን የሚታዘዝ ልጅ አለ፡፡ እንዲሁም አባቱን የማይታዘዝ ልጅ ደግሞ አለ፡፡
ሰውም የሚያገለግለውን ልጁን እንደሚምር፥ እንዲሁ እምራቸዋለሁ። ሚልክያ 3፡17
ህይወታችንን በየጊዜው ካልመረመርንና ካልፈተሽን ግን ካላስተዋልን ማመፃችንን የምናውቀው ከእለታት አንድ ቀን ከረፈደ በኋላ ነው፡፡ ስለዚህ አስተውሉ የሚለው ጥሪ መስማት ወይም ልባችሁን በመንገዳችሁ አድርጉ የሚለው ትእዛዝ መታዘዝ በጣም አስፈላጊ ነው፡፡
ኢየሱስ ስለዘሪው ምሳሌ ሲያስረዳ ቃሉ ሲዘራበት ሙሉ ፍሬ የሚያፈራው አይነት ልብን ሲናገር የሚያስተውል ብሎ ይገልፀዋል፡፡ ማስተዋል ማለት ደግሞ በቀጣይነት ማስታወስ አለመርሳት ሁሌ ማሰብ ከአእምሮ አለመጥፋት በምንወስነው ውሳኔ ሁሉ ማገናዘብ ከግምት ውስጥ መክተት ማለት ነው፡፡
በመልካም መሬት የተዘራውም ይህ ቃሉን ሰምቶ የሚያስተውል ነው፤ እርሱም ፍሬ ያፈራል አንዱም መቶ አንዱም ስድሳ አንዱም ሠላሳ ያደርጋል። ማቴዎስ 13፡23
ስለዚህ ነው በየጊዜው ከምንሰራው ከማንኛውም ነገር አለፍ ብለን ራሳችንን ማየት ያለብን፡፡ በተለይ በዚህ በፈጣንና ለማሰብ ጊዜ በማይሰጥ ዘመን ጊዜያችንን መስዋእት በማድረግ ጊዜ ወስደን የምናስብበትን ሁኔታ ማመቻቸት ይገባናል፡፡
በሃይማኖት ብትኖሩ ራሳችሁን መርምሩ፤ ራሳችሁን ፈትኑ፤ 2ኛ ቆሮንቶስ 13፡5
በየጊዜው የማይፈተን ህይወት በትክክለኛ መንገድ ላይ እንዳለ ምንም ማረጋገጫ የሌለው የብክነት ህይወት ነው፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ማካፈል share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #ልብ #መዳን #እምነት #ማስተዋል #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #የዘላለምህይወት #ፅናት #ማሰብ #መሪ

Friday, October 7, 2016

የህይወት ሚዛን

ህይወት ታላቅ ሃላፊነት ነው፡፡ ህይወትን ትልቅ ሃላፊነት ያደረገው ምክኒያቱ ሚዛኑን ጠብቀን በጥንቃቄ የምንኖረው ስለሆነ ነው፡፡
ለምሳሌ በተለይ በዚህ ዘመን እውቀት ማግኘት ቀላል ነው፡፡ ነገር ግን በጥበብ አመዛዝኖ ለሌሎች በሚጠቅም ሁኔታ እውቀትን መተግበር ሚዛናዊነትን ይጠይቃል፡፡
ስለዚሁ እኛ ደግሞ ይህን ከሰማንበት ቀን ጀምረን የፈቃዱ እውቀት መንፈሳዊ ጥበብንና አእምሮን ሁሉ እንዲሞላባችሁ እየለመንን፥ ስለ እናንተ ጸሎትን አልተውንም፤ ቆላስይስ 1፡9
ስለዚህ ነው ህይወት የሚዛናዊነት ጉዞ ነው የሚባለው፡፡ መፅሃፍ ቅዱስ ባልንጀራህን እንደራስህ አድርገህ ውደድ ማለቱ በአንተና በሌላው መካከል ያለውን ሚዛናዊነት ጠብቅ ማለቱ ነው፡፡ ታዲያ ራስ ወዳድነት የሚባለው ይህ ሚዛን ሲጣስ ሲሆን ህይወት በአንድ ወገን ብቻ ሲያጋድል ህይወት ሚዛኑንና ትርጉሙን ያጣል፡፡
እርሱም መልሶ፦ ጌታ አምላክህን በፍጹም ልብህ በፍጹም ነፍስህም በፍጹም ኃይልህም በፍጹም አሳብህም ውደድ፥ ባልንጀራህንም እንደ ራስህ ውደድ አለው። ሉቃስ 10፡27
መፅሃፍ ቅዱስ ስለኑሮ እንኳን ሲናገር በመጠኑ ኑሩ ንቁም ይላል፡፡ ያ ማለት ለህይወታችን የሚያስፈልገውን መጠቀምና ለህይወት በሚያስፈልገን ነገር ብቻ መወሰን እንዳለብን እያስገነዘበ ሲሆን ህይወትን ከመሰረታዊ ፍላጎት በላይ ሚዛኑን አለማሳለፍ ማለት ነው፡፡ ምንም መልካም ነገር ከመጠን ሲያልፍ ጎጂ ይሆናል፡፡ የኑሮዋችንን ሚዛናዊነቱን ስንጠብቅ ብቻ ነው ከመጠን የማናልፈው ለሌሎችም በረከት መሆን የምንችለው፡፡
በመጠኑ ኑሩ ንቁም፥ባላጋራችሁ ዲያብሎስ የሚውጠውን ፈልጎ እንደሚያጋሳ አንበሳ ይዞራልና፤ 1ኛ ጴጥሮስ 5፡8
መፅሃፍ ቅዱስ ተቆጡ ብሎ ይፈቅድልንና ነገር ግን ቁጣችን ከመጠኑ እንዳያልፍ ሚዛኑን እንድንጠብቅ ያስተምረናል፡፡ ቁጣችን ከቁጥጥር ወጥቶ ሃጢያት እስኪያሰራን መሄድ እንደሌለበት መፅሃፍ ቅዱስ ያስጠነቅቃል፡፡ የሰው ቁጣ የእግዚአብሄርን ፅድቅ አይሰራም በማለት ቁጣ ሚዛናዊ መሆን እንዳለበት ያሳየናል፡፡ ምክኒያቱም ቁጣ ሊሰራ የሚችለውም ሊሰራ የማይችለውም ነገር እንዳለ እያስተማረ ሚዛኑን እንዳንስት ያሳስበናል፡፡
ተቆጡ ኃጢአትንም አታድርጉ፤ በቁጣችሁ ላይ ፀሐይ አይግባ፥ ለዲያብሎስም ፈንታ አትስጡት። ኤፌሶን 4፡26-27
እውነትን ስንናገር እንኳን እውነት ክቡር ሆኖ ሳለ በፍቅር እንድናደርገው ያስተምራል፡፡ እውነትና ምህረት ሚዛኑን ከሳተ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ እንደሚያመዝን ያስተምረናል፡፡ ነገር ግን እውነትን በፍቅር እየያዝን በነገር ሁሉ ወደ እርሱ ራስ ወደሚሆን ወደ ክርስቶስ እንደግ፤ ኤፌሶን 4፡15
ኢየሱስ ይመጣል ነገር ግን ኢየሱስ ስለሚመጣና ምልክቶች እየታዩ ስለሆነ እጃችንን አጣጥፈን እንቀመጥም፡፡ ኢየሱስ ይመጣል ወንጌልን በትጋት እንሰራለን፡፡ ማራናታ ኢየሱስ ሆይ ና እንላለን፡፡ ከመምጣቱ በፊት በትጋት ወንጌልን ለመስራተ እንሮጣለን፡፡
ለቤተስብ ብለን ቅድሚያ የምንሰጥበት ጊዜ አለ ፡፡ ለአገልግሎት ቅድሚያ የምንሰጥበት ጊዜ አለ፡፡ ለግል መንፈሳዊ ህይወታቸን ቅድሚያ የምንሰጥበት ጊዜ አለ፡፡ ሌሎችን ለማገልገል ቅድሚያ የምንሰጥበት ጊዜ አለ፡፡ ይህን የህይወትን ሚዛናዊነት ለመጠበቅ ሁሉንም በልክ አድርግ ያለው የሃዋሪያው ጳውሎስ ምክር በጣም ወሳኝ ነው፡፡
አንተ ግን ነገርን ሁሉ በልክ አድርግ፥ መከራን ተቀበል፥ የወንጌል ሰባኪነትን ሥራ አድርግ፥ አገልግሎትህን ፈጽም። ሉቃስ 10፡5
ሚዛኑን የሚጠብቅ ሰው አንዴ ሚዛኔን ጠብቄያለሁ አሁን መጠንቀቅ የለብኝም እንደማይል በህይወትም ሚዛን መጠበቅ የሁልጊዜ ሃላፊነት እንደሆነ እናስተውላለን፡፡ በየትኛውም ፅንፍ ሳይያዙ በግራም ጉድጓድ ሳይገቡ በቀኝም ጉድጓድ ሳይገቡ በመሃል መንገድ መጓዝ ጤናና ብስለት ነው፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ማካፈል share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #ሚዛን #በመጠን #ራእይ #መዳን #እምነት #በልክ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #የዘላለምህይወት #ፅናት #ትግስት #መሪ

♫ Fikiru Nektogn, Vol. 3 - Solomon Yirga. Listen @cdbaby

♫ Fikiru Nektogn, Vol. 3 - Solomon Yirga. Listen @cdbaby: Click to listen at CDBaby

የአንድነት ጥሪ

እንግዲህ በጌታ እስር የሆንሁ እኔ በተጠራችሁበት መጠራታችሁ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ፤ በትሕትና ሁሉና በየዋህነት በትዕግሥትም፤ እርስ በርሳችሁ በፍቅር ታገሡ፤ በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ።ኤፌሶን ሰዎች 4፡1-3

እግዚአብሄር የተለያየ አድርጎ ፈጥሮናል፡፡ እግዚአብሄር ለመንግስtu እንድንኖርና እንድናገለግል ጠርቶናል፡፡ ስለዚህም ነው አንድነት ያስፈለገው፡፡ እያንዳንዳችን ውስጥ ስጦታ አለ፡፡ እያንዳንዳችን ውስጥ ለእግዚአብሄር መንግስት የሚጠቅም የተለያየ ስጦታ አለ፡፡
በአንድነት መኖር በአንድነት መስራት ከፍተኛ ጥቅም አለው፡፡ እግዚአብሄር ለእኔ የሚጠቅመውን ነገር ነው በወንድሜ ውስጥ ነው ያስቀመጠው፡፡ በእኔ ውስጥ ያስቀመጠው ደግሞ ለወንድሜ የሚጠቅመውን ነገር ነው፡፡ ወንድሜን በጣልኩ መጠን አንድ የአካል ክፍሌን እጥላለሁ፡፡


አንድ ሰው እንዴት ሺህን ያሳድድ ነበር? ሁለቱሳ እንዴት አሥሩን ሺህ ያሸሹ ነበር? ዘዳግም 32፡30

በአንድነት መኖርና ማገልገል ደግሞ እኛን የማይመስለንምን መቀበል ትግስትንና ትህትናን ይጠይቃል፡፡ በአንድነት መኖር ሌላውን ወንድማችንንም እግዚአብሄር እንደሚመራው ማመንን ይጠይቃል፡፡ በአንድነት መኖር በወንድማችን ውስጥ ባለው እምቅ ሃይል ማመን ይጠይቃል፡፡
በክርስቶስም አንዳች ምክር ቢሆን፥ የፍቅር መጽናናት ቢሆን፥ የመንፈስ ኅብረት ቢሆን፥ ምሕረትና ርኅራኄ ቢሆኑ፥ ደስታዬን ፈጽሙልኝ፤ በአንድ አሳብ ተስማሙ፥ አንድ ፍቅር አንድም ልብ አንድም አሳብ ይሁንላችሁ፤ ፊልጵስዩስ 2፡1-2
እንግዲህ በጌታ እስር የሆንሁ እኔ በተጠራችሁበት መጠራታችሁ እንደሚገባ ትመላለሱ ዘንድ እለምናችኋለሁ፤ በትሕትና ሁሉና በየዋህነት በትዕግሥትም፤ እርስ በርሳችሁ በፍቅር ታገሡ፤ በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ። በመጠራታችሁ በአንድ ተስፋ እንደ ተጠራችሁ አንድ አካልና አንድ መንፈስ አለ፤ አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት፤ ከሁሉ በላይ የሚሆን በሁሉም የሚሠራ በሁሉም የሚኖር አንድ አምላክ የሁሉም አባት አለ። ኤፌሶን 4:1-6
የጸጋም ስጦታ ልዩ ልዩ ነው መንፈስ ግን አንድ ነው፤ አገልግሎትም ልዩ ልዩ ነው ጌታም አንድ ነው፤ አሠራርም ልዩ ልዩ ነው፥ ሁሉን በሁሉ የሚያደርግ እግዚአብሔር ግን አንድ ነው። 1ኛ ቆሮንቶስ 12፡4-6
አይሁድ ብንሆን የግሪክ ሰዎችም ብንሆን ባሪያዎችም ብንሆን ጨዋዎችም ብንሆን እኛ ሁላችን በአንድ መንፈስ አንድ አካል እንድንሆን ተጠምቀናልና። ሁላችንም አንዱን መንፈስ ጠጥተናል። አካል ብዙ ብልቶች እንጂ አንድ ብልት አይደለምና። እግር፦ እኔ እጅ አይደለሁምና የአካል ክፍል አይደለሁም ብትል፥ ይህን በማለትዋ የአካል ክፍል መሆንዋ ይቀራልን? ጆሮም፦ እኔ ዓይን አይደለሁምና የአካል ክፍል አይደለሁም ቢል፥ ይህን በማለቱ የአካል ክፍል መሆኑ ይቀራልን? አካል ሁሉ ዓይን ቢሆን መስማት ወዴት በተገኘ? ሁሉም መስማት ቢሆን ማሽተት ወዴት በተገኘ? አሁን ግን እግዚአብሔር እንደ ወደደ ብልቶችን እያንዳንዳቸው በአካል አድርጎአል። 1ኛ ቆሮንቶስ 12፡13-18
ከእርሱም የተነሣ አካል ሁሉ እያንዳንዱ ክፍል በልክ እንደሚሠራ፥ በተሰጠለት በጅማት ሁሉ እየተጋጠመና እየተያያዘ፥ ራሱን በፍቅር ለማነጽ አካሉን ያሳድጋል። ኤፌሶን 4፡16
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ማካፈል share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #ራእይ #መዳን #እምነት #አንድነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ህብረት #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #የዘላለምህይወት #ፅናት #ትግስት #መሪ

Thursday, October 6, 2016

ምኑ ነው አዲስ?

ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል። 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡17
ስለሃጢያቱ በመስቀል ላይ ዋጋ የከፈለውን ኢየሱስን የተቀበለ ሰው ሁሉ አዲስ ፍጥረት ነው፡፡ አዲሱ ሰው እርጅናና ድካም የማያውቀው አዲስ ፍጥረት ነው፡፡ ኢየሱስን እንደ አዳኙና የህይወቱ ጌታው አድርጎ የተቀበለ ሰው አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል፡፡ ግን አዲስ የሆነው ምንድነው ?
  • ልጅነቱ አዲስ ነው፡፡ ሰው በሃጢያት እስራት እያለ የእግዚአብሄር ልጅ አልነበረም፡፡ እውነት ነው የእግዚአብሄር ፍጥረት ነው የእግዚአብሄር ልጅ ግብን አልነበረም፡፡ ሰው በአመፅ ሲኖር የዲያቢሎስ ልጅ ነው፡፡
እናንተ ከአባታችሁ ከዲያብሎስ ናችሁ የአባታችሁንም ምኞት ልታደርጉ ትወዳላችሁ። እርሱ ከመጀመሪያ ነፍሰ ገዳይ ነበረ፤ እውነትም በእርሱ ስለ ሌለ በእውነት አልቆመም። ሐሰትን ሲናገር ከራሱ ይናገራል፥ ሐሰተኛ የሐሰትም አባት ነውና። ዮሃንስ 8፡44
ወዳጆች ሆይ፥ አሁን የእግዚአብሔር ልጆች ነን፥ ምንም እንደምንሆን ገና አልተገለጠም። 1ኛ ዮሃንስ 3፡2
  • ወዳጅነታችን አዲስ ነው፡፡ ሰው ከእግዚአብሄር ጋር ወዳጅ አልነበረም፡፡ ሰው የእግዚአብሄር ጠላት ነበረ፡፡ አሁን ግን ሰው በክርስቶስ የእግዚአብሄር ወዳጅ መሆን ይችላል፡፡
ጠላቶች ሳለን ከእግዚአብሔር ጋር በልጁ ሞት ከታረቅን፥ ይልቁንም ከታረቅን በኋላ በሕይወቱ እንድናለን፤ ሮሜ 5፡10
ከእንግዲህ ወዲህ ባሮች አልላችሁም፤ ባርያ ጌታው የሚያደርገውን አያውቅምና፤ ወዳጆች ግን ብያችኋለሁ፥ ከአባቴ የሰማሁትን ሁሉ ለእናንተ አስታውቄአችኋለሁና። ዮሃንስ 15፡15
  • ህያውነታችን አዲስ ነው፡፡ ሰው ቆሞ ይሂድ እንጂ በእግዚአብሄር እይታ ሙት ነበረ፡፡ ሰው በሃጢያት ምክኒያት ለዘላለም ከእግዚአብሄ ተለይቶ ነበረ፡፡ ሰው ክርስቶስን በመቀበል እግዚአብሄር ይቀበለዋል፡፡ ለዘላለም ከእግዚአብሄር ጋር ይኖራል፡፡
በበደላችሁና በኃጢአታችሁ ሙታን ነበራችሁ፤ ኤፌሶን 2፡1
ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥ ኤፌሶን 2፡5
  • የሰይጣን መጠቀሚያ ነበርን፡፡ የምንኖረው በሰይጣን ፈቃድ ነበር፡፡ አሁን ግን ከሰይጣን ግዛት ወጥተናል፡፡ እኛ ስፍራ ሰጥተነው ካልሆነ ሰይጣን በእኛ ላይ ምንም ስልዕጣን የለውም፡፡
በዚህ ዓለም እንዳለው ኑሮ፥ በማይታዘዙትም ልጆች ላይ አሁን ለሚሠራው መንፈስ አለቃ እንደ ሆነው በአየር ላይ ሥልጣን እንዳለው አለቃ ፈቃድ፥ በፊት ተመላለሳችሁባቸው። ኤፌሶን 2፡2
እነሆ፥ እባቡንና ጊንጡን ትረግጡ ዘንድ፥ በጠላትም ኃይል ሁሉ ላይ ሥልጣን ሰጥቻችኋለሁ፥ የሚጐዳችሁም ምንም የለም። ሉቃስ 10፡19
  • ሰላማችንና መታረቃችን አዲስ ነው፡፡ የቁጣ ልጆች ነበርን፡፡ እግዚአብሄር በሃጢያታችንና በአመፃችን ደስተኛ አልነበረም፡፡ አሁን እግዚአበሄ ተቀብሎናን ኢየሱስ በመስቀል ላይ በሰራው ስራ እግዚአብሄር በእኛ ደስተኛ ነው፡፡ እግዚአብሄር ረክቷል፡፡
በእነዚህም ልጆች መካከል እኛ ሁላችን ደግሞ፥ የሥጋችንንና የልቡናችንን ፈቃድ እያደረግን፥ በሥጋችን ምኞት በፊት እንኖር ነበርን እንደ ሌሎቹም ደግሞ ከፍጥረታችን የቁጣ ልጆች ነበርን። ኤፌሶን 2፡3
እርሱ ሰላማችን ነውና፤ ሁለቱን ያዋሐደ በአዋጅ የተነገሩትንም የትእዛዛትን ሕግ ሽሮ በመካከል ያለውን የጥል ግድግዳን በሥጋው ያፈረሰ፤ ይህም ከሁለታቸው አንድን አዲስን ሰው በራሱ ይፈጥር ዘንድ ሰላምንም ያደርግ ዘንድ፥ 2ኛ ቆሮንጦስ 5፡14-15
  • ተስፋችን አምላካችን አዲስ ነው፡፡ ካለ እግዚአብሄር ካለተስፋ ነበርን፡፡ አሁን ግን አምላክ አለን፡፡ አሁን ግን ተስፋችን ሙሉ ነው፡፡
በዚያ ዘመን ከእስራኤል መንግሥት ርቃችሁ ለተስፋውም ቃል ኪዳን እንግዶች ሆናችሁ በዚህም ዓለም ተስፋን አጥታችሁ ከእግዚአብሔርም ተለይታችሁ ያለ ክርስቶስ ነበራችሁ። ኤፌሶን 2፡12 
  
መጥቶም ርቃችሁ ለነበራችሁ ለእናንተ ሰላምን፥ ቀርበው ለነበሩትም ሰላምን የምስራች ብሎ ሰበከ፤ በእርሱ ሥራ ሁላችን በአንድ መንፈስ ወደ አብ መግባት አለንና። እንግዲያስ ከእንግዲህ ወዲህ ከቅዱሳን ጋር ባላገሮችና የእግዚአብሔር ቤተ ሰዎች ናችሁ እንጂ እንግዶችና መጻተኞች አይደላችሁም። ኤፌሶን 2፡17-19 
ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል። 2ኛ ቆሮንቶስ 5፡17
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ 
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#አዲስፍጥረት #አዲስ #መዋጀት #መዳን #ኢየሱስ #ጌታ #መሪነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #መጋቢ #እምነት #ተስፋ #ፍቅር #ጌታ #ሰላም #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ሰላም ትግስት #ልጅ

እኔ ኤልሻዳይ ነኝ

አብራምም የዘጠና ዘጠኝ ዓመት ሰው በሆነ ጊዜ እግዚአብሔር ለአብራም ተገለጠለትና፦ እኔ ኤልሻዳይ ነኝ በፊቴ ተመላለስ፥ ፍጹምም ሁን፤ ዘፍጥረት 17፡1

ሰዎች ብዙ ጊዜ እግዚአብሄር ለእነርሱ ስለሚያደርገግላቸው ነገር በጣም ሲጨነቁ ይታያል፡፡ ሰዎች ብዙ ጊዜያቸውን የሚያጠፉት ስለእግዚአብሄ ድርሻ በመጨነቅ ነው፡፡ ብዙ ጊዜ ትኩረታቸው እግዚአብሄር እንዴት ቃሉን እንደሚፈፅመው በማውጣትና በማውረድ ነው፡፡እግዚአብሄርን ማንም አያስተምረውም፡፡ እንዴት እንደሚፈፅመው ያውቅበታል፡፡
እግዚአብሔር የዘላለም አምላክ፥ የምድርም ዳርቻ ፈጣሪ ነው፤ አይደክምም፥ አይታክትም፥ ማስተዋሉም አይመረመርም። ኢሳያስ 40፡28
የእግዚአብሄርን ድርሻ ለመስራት ስንሞክር የራሳችንን ድርሻ እንረሳለን፡፡ የራሳችን ድርሻ ላይ ብቻ ብናተኩር የእግዚአብሄር ፈቃድ በሙላት በህይወታችን ይፈፀማል፡፡ ወራሽ የለኝም ብሎ እግዚአብሄር ቃል ኪዳኑን እንዴት እንደሚፈፅም ላልተረዳ አብርሃም እግዚአብሄር እንዲህ አለው፡፡
እኔ ኤልሻዳይ ነኝ በፊቴ ተመላለስ፥ ፍጹምም ሁን፤
እግዚአብሔር ስለእኔ አታስብ፡፡ እኔ ሁሉን ቻይ ነኝ፡፡ ከእኔ ጋር ስትነጋገር ውስን ከሆነ ከሰው ጋር እንደምትነጋገር ማሰብ የለብህም፡፡ እኔ ሁሉን እችላለሁ እያለው ነው፡፡ ካንተ የሚጠበቀው ግን በፊቴ መመላለስ ነው፡፡ በፊቴ እንደምትኖር ኑር፡፡
በፊቴ ውጣ በፊቴ ግባ፡፡ እኔ የምታደርገውን ሁሉ ልይልህ፡፡ በምታደርገው ነገር ሁሉ ልምራህ፡፡ በዚህም ፍፁም ሁን፡፡ በዚህም ታዘዘኝ፡፡ በዚህም እኔን ስማኝ እያለ ነው ጌታ፡፡ እግዚአብሄር ስለሚፈፅምላችሁ የተስፋ ቃል አትጨነቁ፡፡
የሚያሳስባችሁ እናንተ እንዴት እንደምትኖሩለት ብቻ ይሁን ፡፡ እርሱ ቃልኪዳኑን ለመፈፀም ፍላጎቱም ችሎታውም አለው፡፡
እኔ ኤልሻዳይ ነኝ በፊቴ ተመላለስ፥ ፍጹምም ሁን፤
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #ፍፁም #ተመላለስ #ኤልሻዳይ #እምነት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Wednesday, October 5, 2016

ቃሉን መተግበር

እግዚአብሄርን ማስደሰት የመጀመሪያ ፍላጎታችን ስለሆነ ልክ የእግዚአብሄርን ቃል ስናገኝ በራሳችን ልንፈፅመው እንሞክራለን፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሄርን ቃል አገኘነው ማለት በራሳችን እናደርገዋለን ማለት አይደለም፡፡
ስለዚህ ነው በህይወታችን ስለ እግዚአብሄር ቃል ስናስብ ከብዛቱ የተነሳ እንዴት እንደምንተገብረው ግራ ይገባናል፡፡ በህይወቴ ከተማርኩት የእግዚአብሄርን ቃል ለመተግበር ከሚረዱ ነገሮች ጥቂቱን ላካፍላችሁ፡-
የእግዚአብሄር ቃል እንድትገብሩ እናንተ ከምትፈልጉት በላይ እግዚአብሄር ይፈልጋል፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል መተግበር ከእግዚአብሄር ጋር አብራችሁ የምታደርጉት እንጂ ብቻችሁን ስትሞክሩ እግዚአብሄር እንደታዛቢ የሚያያችሁ ጉዳይ አይደለም፡፡ ቃሉን በመፈፀም ሂደት እግዚአብሄር ሙሉ በሙሉ አብሮን መስራት ይፈልጋል፡፡
የእግዚአብሄርን ቃል ለመፈፀም መንፈስ ቅዱስ ሊያስታውሰን ሁሌ ከእኛ ጋር አለ፡፡ አንዳንድ ጊዜ ጌታ ሲናገረኝ መንፈስ ቅዱስ ይህንን እንግዲህ በጊዜው አሳስበኝ ብዬ ለእርዳታ ልቤን አነሳለሁ፡፡
አብ በስሜ የሚልከው ግን መንፈስ ቅዱስ የሆነው አጽናኝ እርሱ ሁሉን ያስተምራችኋል እኔም የነገርኋችሁን ሁሉ ያሳስባችኋል። ዮሃንስ 14፡26
ምክኒያቱም መንፈስ ቅዱስ ራሱ ነው ያ ማለት ይህ ማለት ነው ብሎ የሚያስታውሰንና በተግባር የሚያሳየን፡፡
ነገር ግን ይህ በነቢዩ በኢዩኤል የተባለው ነው። ሐዋርያት 2፡16
የእግዚአብሄርን ቃል ማወቃችን ብቻ ሳይሆን እንዴት እንደምንፈፅመው እግዚአብሄር ጥበብን ሊሰጠን ይገባል፡፡ ምን እንደምናደርግ ብቻ ሳይሆን እንዴት እንደምናደረግ የእግዚአብሄር መንፈስ ሊያሳየን በዝርዝር ጉዳዮች ጥበብን ሊሰጠን ይገባል፡፡
የእግዚአብሄርን ቃል መተግበር የምንችለው በራሳችን ጉልበት መታመን ስናቆምና በእርሱ መንፈስ ላይ ሙሉ ለሙሉ ስንደገፍ ብቻ ነው፡፡ በራሳችን ለመተግበር ከሞከርን አንችልም፡፡
የማደርገውን አላውቅምና፤ የምጠላውን ያን አደርጋለሁና ዳሩ ግን የምወደውን እርሱን አላደርገውም። ሮሜ 7፡15
የእግዚአብሄርን ቃል ለመፈፀም በእግዚአብሄር ቃል ከባቢ ውስጥ መሆን ይጠይቃል፡፡ የእግዚአብሄርን ቃል ማሰብና ማሰላሰል ቃሉን እንድንተገብረው ተግባራዊ መረዳት ይሰጠናል እንዲሁም ሃይልን ያስታጥቀናል፡፡ ቃሉን ስናሰላስል ይበልጥ ብርሃን ይሰጠናል ዝርዝር አፈፃፀሙን ያሳየናል፡፡
የዚህ ሕግ መጽሐፍ ከአፍህ አይለይ፥ ነገር ግን የተጻፈበትን ሁሉ ትጠብቅና ታደርግ ዘንድ በቀንም በሌሊትም አስበው፤ የዚያን ጊዜም መንገድህ ይቀናልሃል ይከናወንልሃልም። ኢያሱ 1፡8
በእርግጥ በተረዳነው በእግዚአብሄር ቃል ጀምረን ቃሉን ለማድረግ መነሳት አለብን፡፡ አንዳንዴ የተፃፈውን ቃል ሁሉ ለማድረግ ስናስብ ይጨንቀናል እንዲያውም እግዚአብሄር የማይቻል ነገር እንዳዘዘን ሁሉ ሊሰማን ይችላል፡፡ እግዚአብሄር ያዘዘን ሁሉ የሚቻል ነገር ነው ፡፡ ነገር ግን የእግዚአብሄርን ቃል መፈፀም ያለብን በእርግጥ ለተረዳነው ቅድሚያ በመስጠት መሆን አለበት፡፡ ከሁላችንም እኩል አይጠበቅምንም ከእያንዳንዳችን ግን እንደ መረዳታችን መጠን ይጠበቅብናል፡፡
የጌታውንም ፈቃድ አውቆ ያልተዘጋጀ እንደ ፈቃዱም ያላደረገ ያ ባሪያ እጅግ ይገረፋል፤ ያላወቀ ግን መገረፍ የሚገባውንም ያደረገ ጥቂት ይገረፋል። ብዙም ከተሰጠው ሰው ሁሉ ከእርሱ ብዙ ይፈለግበታል፥ ብዙ አደራም ከተሰጠው ከእርሱ አብዝተው ይሹበታል። ሉቃስ 12፡47-48
ህፃን በወተት እንደሚያድግና ለጠንካራ ምግብ እንደሚዘጋጅ ሁሉ ከተረዳነው ከምናውቅው ጀምረን የእግዚአብሄርን ቃል ስንፈፅም ቃሉን መፈፀማችን መንፈሳዊ ጡንቻችንን ስለሚያጠነክረው እግዚአብሄር ሌሎች ቃሎችን እንድንታዘዛቸው ያሳየናል፡፡
የእግዚአብሄርን ቃል ስንፈፅም እግዚአብሄርን ማመስገን ይኖርብናል፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ