I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ሃሎዊን Halloween የሚባለው በአል በኦክቶበር ወር መጨረሻ ላይ በተለያ የ መልኩ ይከበራል ፤ ባብዛኛው ህዝብ ዘንድ እንደ አንድ ባህል የሚ ከ ብረው ይህ የሃሎዊን በአል ሰዎች ቢገባ...
-
እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ። 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ...
-
እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ። 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ...
-
እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁ...
-
Dhalachuun Yesus Raawwii Raajichaa Ture Kanaafis Waaqayyo ofii isaatii milikkita isiniif in kenna; kunoo, durbi in ulfoofti, ilmas in deess...
-
ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች። ትንቢተ ኢሳይያስ 7፡14 በመጽሃፍ ቅዱስ ነቢዩ ኢሳያስ ስለ ኢየሱስ መወለድ ትንቢትን የተናገ...
-
https://youtu.be/VhF0pSsp14I በቃልኪዳን መነጽር ህይወታችን ማየት አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa ሬማ እምነት አገልግሎት በርሚንግሃም ቤተክርስትያን
Sunday, July 31, 2022
Saturday, July 30, 2022
Wednesday, July 27, 2022
Monday, July 25, 2022
ባለ ጠጋም በውርደቱ ይመካ
የተዋረደው ወንድም ግን በከፍታው፥ ባለ ጠጋም በውርደቱ ይመካ፤ እንደ ሣር አበባ ያልፋልና። ፀሐይ ከትኵሳት ጋር ይወጣልና፥ ሣርንም ያጠወልጋልና፥ አበባውም ይረግፋልና፥ የመልኩም ውበት ይጠፋልና፤ እንዲሁ ደግሞ ባለ ጠጋው በመንገዱ ይዝላል። የያዕቆብ መልእክት 1:9-11
ሁላችንም
በህይወታችን
ከእኛ
የሚበልጥ
የሚያስመካ
ሃያል
ነገርን
እንፈልጋለን፡፡
ነገር
ግን
ያስመካል
ብለን
የምናስበው
ነገር
ሁሉ
የሚያስመካ
አይደለም፡፡
መፅሃፍ
ቅዱስ
በሚታይ
ነገር
የተዋረደ
ወንድም
ሊዋረድ
እንደማይገባው
ያስተምረናል፡፡
በምድራዊ
ነገር
ብዙ
ነገር
የሌለው
ሰው
በውርደቱ
እንዳይዋረድ
መፅሃፍ
ቅዱስ
ያስጠነቅቃል፡፡
በምድራዊ
ህይወት
ደረጃው
ዝቅተኛ
የሆነ
ሰው
ውርደቱን
በሚሸፍን
በእግዚአብሄር
እንዲመካ
ያስተምራል፡፡
በምድራዊ
ነገር
ባለጠጋ
መሆን
ለመመካት
ብቁ
ያልሆነ
ነገር
በመሆኑ
በምድራዊ
ነገር
ባለጠጋ
የሆነ
ሰው
በባለጠግነቱ
እንዳይመካ
መፅሃፍ
ቅዱስ
ይመክራል፡፡
ባለጠጋ
መመካት
ያለበት
የሚያስፈልገውን
በማያጎድልበት
በእግዚአብሄር
ብቻ
ነው፡፡
የእግዚአብሄር
ነገር
ብቻ
እንጂ
በምድር
ላይ
ምንም
የሚያስተማምን
ምንም
ቋሚ
ነገር
የለም፡፡
ብላቴኖች
ይደክማሉ
ይታክቱማል፥
ጐበዛዝቱም
ፈጽሞ
ይወድቃሉ፤
እግዚአብሔርን
በመተማመን
የሚጠባበቁ
ግን
ኃይላቸውን
ያድሳሉ፤
እንደ
ንስር
በክንፍ
ይወጣሉ፤
ይሮጣሉ፥
አይታክቱም፤
ይሄዳሉ፥
አይደክሙም።
ኢሳያስ
40፡30-31
Saturday, July 23, 2022
ስለገንዘብ የመመካት ስጋዊነት
ስለገንዘብ የመመካት ስጋዊነት
ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥየለም። 1 ኛ ዮሀንስ 3:15-16
ስለገንዘብ የመመካት ስጋዊነት ከህፃንነት የሚመነጭ የስጋዊነት ሀጢያት ነው::
ስለገንዘብ የመመካት ስጋዊነት የእግዚአብሔርን ፍቅር በአግባቡ ካለመረዳት የሚመጣ አለመብሰል እንጭጭነትነው::
ሰው በእግዚአብሐር የተወደደበትን ጥልቅ ፍቅር ሲረዳ የገንዘብን ትንሽነት እና ውስንነት ስለሚረዳ በገንዘብውይም በኑሮ ከመመካት የስጋዊነት ሀጢያት ይድናል::
ከክፉ የሚጠብቀውን የሚያኖረውን የእግዚአብሔርን ፍቅር በሚገባ የተረዳ ሰው ስለገንዘብ መመካትያሳፍረዋል::
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናውአይመካ፤ ነገር ግን የሚመካው። ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔንበማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ፤ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር። ኤርሚያስ 9:23-24
ሰው በሚበላው ምግብ ውድነት ከተመካ ስጋዊ ሰው ነው::
ሰው በሚነዳው መኪና ውድነት ከተመካ ስጋዊ ሰው ነው እንጂ መንፈሳዊ ሰው አይደለም::
ሰው ባለመማሩ ካዘነ እና ከተዋረደ መንፈሳዊ ስው አይደለም ማለት ነው::
ሰው ባለው እውቀት ከተመካ ከአለማዊ አስተሳሰብ ያልዳነ ስጋዊ ሰው ነው::
ሰው ባለው ሀብት ከተመካ ስጋዊ ሰው ነው::
ሰው ባለው ዘመድ ከተመካ ስጋዊ ሰው ነው::
ሰው በሚለብሰው ልብስ ውድነት ከተመካ መንፈሳዊ ሰው አይደለም::
ሰው በእግዚአብሔር ሳይሆን በውበቱ ከተመካ እን ደስ ድስ ከተሰኘ ስጋዊ ሰው ነው::
ሰው በድህነቱ ካዘነ እና ከተዋረደ መንፈሳዊ ስው አይደለም ማለት ነው::
በሚኖርበት ቤት ትልቅነት እና ውድነት የሚመካ ሰው መንፈሳዊ አይደለም ማለት ነው::