Popular Posts

Thursday, September 28, 2023

ነገር ግን ደካሞች የሚመስሉ የአካል ብልቶች ይልቁን የሚያስፈልጉ ናቸው፤ ከአካልም ብልቶች ያልከበሩ ሆነው የሚመስሉን በሚበዛ ክብር እናለብሳቸዋለን፥ በምናፍርባቸውም ብልቶቻችን ክብር ይጨመርላቸዋል፤ ክብር ያላቸው ብልቶቻችን ግን ይህ አያስፈልጋቸውም። ነገር ግን ብልቶች እርስ በርሳቸው በትክክል ይተሳሰቡ ዘንድ እንጂ በአካል መለያየት እንዳይሆን፥ ለጎደለው ብልት የሚበልጥ ክብር እየሰጠ እግዚአብሔር አካልን አገጣጠመው። 1ኛ ቆሮንጦስ 12:22-25

 ነገር ግን ደካሞች የሚመስሉ የአካል ብልቶች ይልቁን የሚያስፈልጉ ናቸው፤ ከአካልም ብልቶችያልከበሩ ሆነው የሚመስሉን በሚበዛ ክብር እናለብሳቸዋለን፥ በምናፍርባቸውም ብልቶቻችን ክብርይጨመርላቸዋል፤ ክብር ያላቸው ብልቶቻችን ግን ይህ አያስፈልጋቸውም። ነገር ግን ብልቶች እርስበርሳቸው በትክክል ይተሳሰቡ ዘንድ እንጂ በአካል መለያየት እንዳይሆን፥ ለጎደለው ብልት የሚበልጥክብር እየሰጠ እግዚአብሔር አካልን አገጣጠመው። 1 ቆሮንጦስ 12:22-25

Monday, September 25, 2023

The Bottom Line

 

Our lives should be lived with the intent of fulfilling God's purpose for us, rather than simply existing. That is the final conclusion.

What you do after eating is more important than what you consume, in my opinion.

In comparison to the reason you drive, the car you drive doesn't really matter.

Driving the most expensive car in the world is vanity if you don't truly pursue God's purpose for your life.

To complete God's purpose in our lives, the purpose of our lives is by far more significant than what we wear.

Even if you are the most attractive person alive and fall short of God's plan for your life, you have failed.

If you are the strongest human being but have failed to use your influence to fulfil God’s purpose in your life, your strength is nothing.

If you are the most intelligent person on the planet, but you do not use your knowledge for God's purposes in your life, then your life has failed.

Man is created for God's purpose and for his glory. Every provision and opportunity is meant for the purpose of fulfilling God’s purpose for our lives. 

Abiy Wakuma Dinsa #purpose #success #prosperity #vanity #wisdom #might #riches #God #Jesus 

Thursday, September 21, 2023

የንጉሱ አስደናቂ ታሪክ

 


ከአሥራ ሁለት ወር በኋላ በባቢሎን ቤተ መንግሥት ሰገነት ላይ ይመላለስ ነበር። ንጉሡም፦ ይህች እኔ በጕልበቴ ብርታት ለግርማዬ ክብር የመንግሥት መኖሪያ እንድትሆን ያሠራኋት ታላቂቱ ባቢሎን አይደለችምን? ብሎ ተናገረ። ቃሉም ገና በንጉሡ አፍ ሳለ ድምፅ ከሰማይ ወደቀና፦ ንጉሥ ናቡከደነፆር ሆይ፦ መንግሥት ከአንተ ዘንድ አለፈች ተብሎ ለአንተ ተነግሮአል፤ ልዑሉም በሰዎች መንግሥት ላይ እንዲሠለጥን፥ ለሚወድደውም እንዲሰጠው እስክታውቅ ድረስ ከሰዎች ተለይተህ ትሰደዳለህ፥ መኖሪያህም ከምድር አራዊት ጋር ይሆናል፤ እንደ በሬም ሣር ትበላ ዘንድ ትገደዳለህ፥ ሰባት ዘመናትም ያልፉብሃል አለው። በዚያም ሰዓት ነገሩ በናቡከደነፆር ላይ ደረሰ፤ ጠጕሩም እንደ ንስር፥ ጥፍሩም እንደ ወፎች እስኪረዝም ድረስ ከሰዎች ተለይቶ ተሰደደ፥ እንደ በሬም ሣር በላ፥ አካሉም በሰማይ ጠል ረሰረሰ። ዘመኑም ከተፈጸመ በኋላ እኔ ናቡከደነፆር ዓይኔን ወደ ሰማይ አነሣሁ፥ አእምሮዬም ተመለሰልኝ፤ ልዑሉንም ባረክሁ፥ ለዘላለምም የሚኖረውን አመሰገንሁ አከበርሁትም፤ ግዛቱ የዘላለም ግዛት ነውና፥ መንግሥቱም ለልጅ ልጅ ነውና። በምድርም የሚኖሩ ሁሉ እንደ ምናምን ይቈጠራሉ፤ በሰማይም ሠራዊት በምድርም ላይ በሚኖሩ መካከል እንደ ፈቃዱ ያደርጋል፤ እጁንም የሚከለክላት ወይም፦ ምን ታደርጋለህ? የሚለው የለም። በዚያን ጊዜም አእምሮዬ ተመለሰልኝ፥ ለመንግሥቴም ክብር ግርማዬና ውበቴ ወደ እኔ ተመለሰ፤ አማካሪዎቼና መኳንንቶቼም ፈለጉኝ፥ በመንግሥቴም ውስጥ ጸናሁ፥ ብዙም ክብር ተጨመረልኝ። አሁንም እኔ ናቡከደነፆር የሰማይን ንጉሥ አመሰግናለሁ፥ ታላቅም አደርገዋለሁ፥ አከብረውማለሁ። ሥራው ሁሉ እውነት፥ መንገዱም ፍርድ ነውና፥ በትዕቢትም የሚሄዱትን ያዋርድ ዘንድ ይችላልና። ትንቢተ ዳንኤል 4:29-37


Thursday, September 14, 2023

የእግዚአብሔር #ጸጋ ተገልጦአል

 

ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል ወደ ቲቶ 2፡11-13

ሰዎች ካሉበት ከማንኛውም ጥፋት የሚያድናቸው የእግዚአብሔር ፀጋ ተገልጦዋል፡፡

የሰው ማንኛውም ችግር እና ጥፋት ምንጩ ሃጢያት ነው፡፡ ሃጢያት ሰውን ከእግዚአብሔር  ክብር አዋርዶ እንደሚጠፋ እንስሳት አስመስሎታል፡፡  

ሰው ግን ክቡር ሆኖ ሳለ አያውቅም፤ እንደሚጠፉ እንስሶች መሰለ። መዝሙረ ዳዊት 49፡12

ሃጢያት ሰውን ሁሉ ያዋርዳል ያሳንሳል ያጎሳቁላል፡፡ በአጠቃላይ ሃጢያት ሰውን ባሪያ ያደርጋል፡፡

ኢየሱስ መለሰ፥ እንዲህ ሲል፦ እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ኃጢአት የሚያደርግ ሁሉ የኃጢአት ባርያ ነው።የዮሐንስ ወንጌል 8፡34

ሰውን ከሃጢያት እስራት ነፃ ማውጣት የሚችል ጉልበት ያለው የእግዚአብሔር ፀጋ ብቻ ነው፡፡

የእግዚአብሔር ፀጋ ጉልበት ሃጢያትን ያስክዳል፡፡ የእግዚአብሔር ፀጋ ሃያል የሆነውን አለማዊ ምኞትን ያስንቃል፡፡ የእግዚአብሔር ፀጋ እግዚአብሔርን የመምሰል ሃይልን ይሰጣል፡፡ ፀጋ በፅድቅ እንድንኖር አቅም ይሰጠናል፡፡

ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱስ ክርስቶስን ክብር መገለጥ እየጠበቅን፥ ራሳችንን በመግዛትና በጽድቅ እግዚአብሔርንም በመምሰል በአሁኑ ዘመን እንድንኖር ያስተምረናል ወደ ቲቶ 2፡11-13

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

#ኢየሱስ #ጌታ #እምነት #ሃይል #ወንጌል #ፅድቅ #ሃጢያት #ቤተክርስቲያን #መፅሐፍቅዱስ #ቃል #እግዚአብሔር #መስቀል #አቅም #ጉልበት  


ገንዘብን እንጀራ ላይደለ፥ የድካማችሁንም ዋጋ ለማያጠግብ ነገር ለምን ትመዝናላችሁ? ትንቢተ ኢሳይያስ 55:2

 


Sunday, September 10, 2023

እውነተኛው አዲስ አመት ክፍል 5

 

ስለዚህ ማንም በክርስቶስ ቢሆን አዲስ ፍጥረት ነው፤ አሮጌው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ ሁሉም አዲስ ሆኖአል። 2 ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 517

የሰውን ማንነቱን ፣ ተፈጥሮውን ፣ ባህሪውን ፣ ተስፋውን ፣ ግቡን የሚለውጠው እና የሚያድሰው አዲስ ፍጥረት መሆኑ ነው፡፡ ሰው አዲስ ፍጥረት ካልሆነ አዲስ ወር አዲስ አመት በመጣ ቁጥር አዲስ ነገር መጠበቅ ተመሳይ ነገር እያደረጉ የተለየ ውጤት እንደመጠበቅ ከንቱ ነው፡፡

አዲስ ዘመን እንዲሆን አዲስ ሰው ይጠይቃል፡፡ አዲስ ዘመን ቢመጣም ሰውየው አዲስ ካልሆነ ዋጋ የለውም፡፡

ኢየሱስ አዲስ ነገር በአዲስ መያዣ ውስጥ መቀመጥ እንዳለበት ከዚህ በታች ባሉት ጥቅሶች በማብራሪያ ያስተምራል፡፡ አዲስ አመት አዲስን ሰው ይጠይቃል፡፡ አዲስነት እንዲሰምር ሁለቱም አዲስ መሆን አለባቸው፡፡ አንዱ ብቻ አዲስ ሆኖ ሌላው አሮጌ ከሆነ አይሰራም፡፡

በአረጀ ልብስ አዲስ እራፊ የሚጥፍ የለም፤ ቢደረግ ግን፥ አዲሱ መጣፊያ አሮጌውን ይቦጭቀዋል፥ መቀደዱም የባሰ ይሆናል።በአረጀ አቁማዳም አዲስ የወይን ጠጅ የሚያኖር የለም፤ ቢደረግ ግን፥ የወይን ጠጁ አቁማዳውን ያፈነዳል የወይኑም ጠጅ ይፈሳል አቁማዳውም ይጠፋል አዲሱን የወይን ጠጅ ግን በአዲስ አቁማዳ ያኖራሉ። የማርቆስ ወንጌል 2፡21-22

መልካም አዲስ አመት

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

#ኢየሱስ #ጌታ #ቀን #አመት #ወንጌል #አዲስአመት #ለውጥ #ቤተክርስቲያን #መፅሐፍቅዱስ #ቃል #እግዚአብሔር #መስቀል #እንቁጣጣሽ #ዘመንመለወጫ