I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
በፊቱም ልባችንን እናሳርፋለን፥ እግዚአብሔር ከልባችን ይልቅ ታላቅ ነውና ሁሉንም ያውቃል። 1ኛዮሐንስ 3:19-20
-
ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2 ፣6 7 ክርስቶስ ወደ ምድር የመጣው ስለእኛ ነው። ክርስቶስ ወደ ምድር የመጣው እኛ በሃጢያታችን...
-
Kanaafis Waaqayyo ofii isaatii milikkita isiniif in kenna; kunoo, durbi in ulfoofti, ilmas in deessi, maqaa isaas Amaanu'el jettee in mo...
-
Name it claim it Take it! “So Jesus answered and said to them, “Have faith in God. For assuredly, I say to you, whoever says to this mount...
-
የብልጽግና ወንጌል ምሥጢር ሲገለጥ በወንጌል አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና። ወደ ሮሜ ሰዎች 1፡16 ወንጌል በሃጢያታቸው ምክኒያት ለዘላለም ከእ...
-
ጸሎት ከእግዚአብሄር ጋር መነጋገር ነው። ጸሎት ሊደረግ የሚችለው ከእግዚአብሄር ጋር በመግባባት ብቻ ነው። ጸሎት የሚሰምረው እንደ እግዚአብሄር አሳብ ስንጸልይ ብቻ ነው። በአጠቃላይ ለእግዚአብሄር ያለን አመለካከት ...
-
የምንሞትለት እንጂ የምንገድልለት አምላክም ሆነ ሀይማኖት የለንም! አምላክ ሀያል ነው የእኛ እርዳታ አይፈልግም። እንዲገድሉለት የሰውን እርዳታ የሚፈልግ ሀይማኖት እውነተኛ ሀይማኖት አይደለም። የሰውን እርዳታ የሚፈልግ...
-
እግዚአብሄር - አባት የሁልጊዜ ነው፡፡ አባት ስሜቱን ዋጥ ያደርጋል፡፡ አባት ተለዋዋጭ ስሜቱን አይከተልም፡፡ አባት በመርህ ይመራል፡፡ ሕፃን ተወልዶልናልና፥ ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና፤ አለቅነትም በ...
-
ብዙ ጊዜ የምናተኩረው በክርስቶስ ስለተደረገልን ነገር ነው፡፡ በክርስቶስ የተደረገልን ነገር ሁሉ ያልለፋንበት ስጦታ ነው፡፡ በክርስቶስ ይህ ሁሉ ነገር ተፈደርጎልንም ለሃላፊነት የማንበቃ ህፃናት ልንሆን እንችላለን፡፡ ...
-
God created man in his image, after his likeness. One of the most important characters God wants to see in us in gentleness. Gentleness c...
Wednesday, September 9, 2026
እውነተኛው የዘመን አቆጣጠር
ይህ ወር የወሮች መጀመሪያ፤ የዓመቱም መጀመሪያ ወር ይሁናችሁ። ኦሪት ዘጸአት 12:2
እውነተኛው አዲስ አመት የሚባለው ቃሉን ሰምተን ነጻ የምንወጣበትን ጊዜ ነው። እውነተኛው ዘመን መለወጫ የሚባለው ቃሉን ሰምተን በቃሉ የዳንንበት ቀን ነው።
ዘጸአት ምዕራፍ 12 በአጠቃላይ እግዚአብሔር ለእስራኤል ከግብፅ ነፃ በወጡበት ወቅት አዲስ ጅምር ያደረገበት ምዕራፍ ነው።
ዘጸአት 12፡2 — እግዚአብሔር ለሙሴና ለአሮን እንዲህ አላቸው፦ «ይህ ወር ለእናንተ የወሮች መጀመሪያ፣ የዓመቱም የመጀመሪያ ወር ይሁንላችሁ።»
እስራኤላዊያን ሊያድናቸው የመጣውን የእግዚአብሄር ቃል ሰምተው ከግብጽ ባርነት ነጻ የወጡበትን ቀን የወሩ መጀመሪያ ወሩን ደግሞ የአመቱ መጀምሪያ እንዲሆን ተነገራቸው።
ቀናቸውን እና ወራቸውን አንድ ብለው የጀመሩት ከነጻነታቸው ቀን ጀምረው ነው።
ዘጸአት 13፡3–4 ደግሞ ይህንን አዲስ ቀን እና አዲስ ወር ከግብፅ ነፃ ከመውጣታቸው ጋር ይገናኛል።
በመጽሐፍ ቅዱስ እይታ፣ «አዲሱ ዓመት» የሚቀርበው እንደ ቀላል የቀን መቁጠሪያ ለውጥ ብቻ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ቤዛነትና ነፃ ማውጣት የተፈጠረ አዲስ ጅምር እንደሆነ ነው።
ዛሬም እውነተኛ ነጻነት የእግዚአብሄርን ቃል ሰምተን ነጻ የምንወጣበት ነጻነት ነው።
ኢየሱስም ያመኑትን አይሁድ፦ እናንተ በቃሌ ብትኖሩ በእውነት ደቀ መዛሙርቴ ናችሁ፤ እውነትንም ታውቃላችሁ እውነትም አርነት ያወጣችኋል አላቸው። የዮሃንስ ወንጌል 8፡31፣ 32
አዲስ ዘመንም የእግዚአብሄርን ቃል ሰምተን ነጻ የወጣንበትን ቀን ነው።
እውነተኛው ዘመን መለወጫ ደግሞ የዘመን መቁጠሪያ ካላንደር ሳይሆን በእግዚአብሄር ቃል ነጻ የምትወጡበት ቀን ነው።
ነገር ግን ነጻ የሚያወጣውን ፍጹሙን ሕግ ተመልክቶ የሚጸናበት፥ የያዕቆብ መልእክት 1:25
በቃሉ ነጻ ለወጣ ሰው ጷጉሜ 5 የዘመን መለዋጫ ነው። የእግዚአብሄርን ቃል ሰምቶ ነጻ ለማይወጣበት ሰው ግን በመስከረም 1 እንኳን ዘመኑን አይለወጥም።
ስለዚህ ጥያቄው የእግዚአብሄርን ቃል በመስማት እና በማድረግ ዘመናችሁን ለመለወጥ ተዘጋጅታችኋል ወይስ ዘመኑ በራሱ ህይወቴን ይለወጣል ብላችሁ በከንቱ ተስፋ እያደረጋችሁ ነው ?
ህይወትን የሚለወጥ የእግዚአብሁሄር ቃል ብቻ ነው። ቀን ያው የተለመደው ተመሳሳይ ሰኞ ማክሰኞ ሮብ ሃሙስ አርብ ቅዳሜ እሁድ ነው። የእግዚአብሄር ቃል ህይወታችንን ካልለወጠ ቀን ህይወትን ሊለውጥ አይችልም።
አዲስ አመት ህይወታችን በእግዚአብሄር ቃል እንዲለወጥ የመንፈቅድበት አዲስ እድል እንጂ በራሱ የህይወት ለወጥ አይደለም።
መልካም አዲስ አመት መልካም አዲስ ህይወት
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
Subscribe to:
Post Comments (Atom)
No comments:
Post a Comment