I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
Name it claim it Take it! “So Jesus answered and said to them, “Have faith in God. For assuredly, I say to you, whoever says to this mount...
-
አንድ አረጋዊ በ ባሕር ዳርቻ መንገድ ላይ እየሄደ እያለ አንድ ወጣት አጎንብሶ የሆነ ነገር በማንሳት ወደ ውቆያኖስ ውስጥ ሲጥል ከሩቅ ያየዋል፡፡ እየተጠጋ ሲሄድ እያነሳ ወደውሃ ውስጥ የሚመልሰው ኮከበ...
-
የተጠሩ ብዙዎች፥ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸውና። የማቴዎስ ወንጌል 22፡14 እግዚአብሄር ቅን ፈራጅ ነው፡፡ እግዚአብሄር እውነተኛ ዳኛ ነው፡፡ እግዚአብሄር ለሁሉም ሰው እኩል እድልን ይሰጣል፡፡ እግዚአብ...
-
እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ክፉውን አትቃወሙ፤ ዳሩ ግን ቀኝ ጉንጭህን በጥፊ ለሚመታህ ሁሉ ሁለተኛውን ደግሞ አዙርለት፤ ማቴዎስ 5፡39 በህይወቱ የሚያየውን ክፉ ሁሉ በክፉ ለመመለስ የሚያስብ ሰው ...
-
በሃጢያት ጨለማ በጠፋሁ ጊዜ ፈልጎ ያገኘኝን የክርስቶስን እውቀት ብርሃን በልቤ ያበራን እግዚአብሄርን ማመስገን አለብኝ፡፡ ሳላውቀው ሳልረዳው ስለሃጢያቴ የሞተልኝን እግዚአብሄርን የማመስገን ግዴታ አለብኝ፡፡ ከልጅነቴ...
-
የእናንተ ሥርና መሠረት በፍቅር ይጸና ዘንድ፥ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ ከፍታውም ጥልቅነቱም ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል፥ ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር ለማወቅ ...
-
ስለኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን እምነት ሲነሳ ስለቅዱሳንና መላእክት ስግደት ፣ ስለማርያም አማላጅነት ስለመሳሰሉት ይነሳል፡፡ ይህ ሁሉ ግን ዋና ነገር አይደለም፡፡ ምንም እንኳን የምናምናቸው መፅሃፍ ቅዱሳዊ ያልሆኑ ነገሮች...
-
በሰው ህይወት ውስጥ ግንኙነት እጅግ በጣም አስፈላጊ እንደመሆኑ መጠን ግንኙነት በትክክል እንዲሰራ የሚያስችለው ነዳጁ ፍቅር ነው፡፡ ፍቅር በጣም አስፈላጊ ነገር ቢሆንም ስለፍቅር ብዙ የተባለና የተፃፈ ቢሆንም ...
Monday, February 28, 2022
Saturday, February 26, 2022
Tuesday, February 22, 2022
Friday, February 18, 2022
Sunday, February 13, 2022
የፍቅር ምንጭ
ስለ ፍቅር ብዙ ይዘከራል ይወራል፡፡
ሁሉም
ሰው ይህ የሚዘመርለትንና የሚሰበክለትን ፍቅር ማወቅ ፣ መኖር እና ማጣጣም ይፈልጋል፡፡ ነገር ግን ወደ ተግባር ሲመጣ ፍቅር በተግባር
ሊተረጎም የማይችል ረቂቅ ነገር ብቻ ይሆንበታል፡፡
ሰው
ደግሞ እውነተኛውን ፍቅርን ካልተረዳ ተመሳሳዩን ምኞትን እንደፍቅር ይዞት ባነሰ ነገር ረክቶ ይኖራል፡፡
ፍቅር
ግን ምኞት አይደለም፡፡ ፍቅር ስሜት አይደለም፡፡ ፍቅር ከፍ ያለ የህይወት ደረጃ ነው፡፡
ስለፍቅር
የሚናገሩትን መፅሃፍት በማንበብ ፍቅር አይመጣም፡፡ ፍቅር ከሰው አይመጣም፡፡ ሰው ራሱ ፍቅርን የተራበ እና ፍቅር የሚያስፈልገው
ፍጥረት ስለሆነ ፍቅርን በራሱ ሊሰጥ አይችልም፡፡
ፍቅር
የሚመጣው ፍቅር ከሆነው ከእግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
እግዚአብሔር
ፍቅር ነው፥ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል። 1ኛ ዮሐንስ 4፡16
ፍቅርን
ሊያውቅ በፍቅር ሊኖር የሚችለው በእግዚአብሄር የሚኖር ሰው እግዚአብሄርም በእርሱ የሚኖርበት ሰው ብቻ ነው፡፡
ሰው
ፍቅርን ከእግዚአብሄር ካላገኘ ምኞትን እንጂ ፍቅርን በፍፁም ሊያውቀው አይችልም፡፡
ሰው
ከእግዚአብሄር ፍቅርን ካልተቀበለ ፍቅርን ተቀብሎ አያውቅም፡፡ ሰው በእግዚአብሄር ፍቅር ጉልበት ካላገኘ በእውነተኛ ፍቅር ሌላውን
የሚወድበት አቅም አይኖረውም፡፡
ሰው
ምክኒያታዊ ያልሆነውን እውነተኛውን ፍቅርን መማር የሚችለው ፍቅር ከሆነው ከእግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
የእግዚአብሄርን
ፍቅር የቀመሰ ሰው ብቻ እውነተኛውን ፍቅር ያውቃል፡፡
የእግዚአብሄርን
ፍቅር የቀመሰ ሰው ብቻ የተቀበለውን ፍቅር ለሌላው መስጠት ይችላል፡፡
በተሰጠንም
በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን ስለ ፈሰሰ ተስፋ አያሳፍርም። ሮሜ 5፡5
በእግዚአብሄር
ፍቅር የረካ ሰው ብቻ ሌላውን ሰው በፍቅር ሊያረካ ይችላል፡፡
ሰው
የእግዚአብሄርን ፍቅር በተቀበለ መጠን የእንካ በእንካ ያልሆነውን ፍቅር ለሌላው መስጠት ይችላል፡፡
Abiy Wakuma Dinsa አቢይ ዋቁማ
ዲንሳ
ለተጨማሪ
ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
ለቪዲዮ
መልእክቶች
https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ
#ጌታ #እምነት #ፍቅር #ስር #መሰረት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #ቸርነት #ትግስት #ከቅዱሳንሁሉጋር #መታበይ #መመካት #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ