I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ጸሎት ከእግዚአብሄር ጋር መነጋገር ነው። ጸሎት ሊደረግ የሚችለው ከእግዚአብሄር ጋር በመግባባት ብቻ ነው። ጸሎት የሚሰምረው እንደ እግዚአብሄር አሳብ ስንጸልይ ብቻ ነው። በአጠቃላይ ለእግዚአብሄር ያለን አመለካከት ...
-
… From Oppressive Obligations to Incredible Opportunities The phone isn’t just ringing, it seems to be screaming. You’ve got yet another...
-
ፈተና ለእኛ መልስ የሌለው ጥያቄ ነው፡፡ በህይወት መልስ የሌለው ጥያቄ የለም፡፡ በህይወት መውጫ የሌለው ፈተና የለም፡፡ ፈተና የለም ማለት ስህተት እንደሆነ ሁሉ ፈተናው መልስ የለውም ማለት እንዲሁ ስህተት ነው፡፡ ፈተ...
-
God created mankind simple. He created him and commanded him to eat everything except the tree of the knowledge of good and evil. But m...
-
ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን...
-
There are different seasons in our lives. There is a season to live with others there is a season to go our way. Seasons definitely cha...
-
በተለያየ ጊዜ በህይወታችን የተለያዩ ተግዳሮቶች ይመጣሉ፡፡ ታዲያ ይህን አልፈው ይሆን ብለን የምናስብበት ውጥረት በህይወታችን ይመጣል፡፡ እንደዚህ አይነት ውጥረት በህይወታችን ሲገጥመን "በምድር ላይ ያለሁት ለ...
-
ኢየሱስ ክርስቶስን አምኖ በተቀበለ ሰው ላይ መርገም ሊሰራበት ወይንም ደግሞ ከዘር ማንዘር ሊተላለፍበት ይችላል ወይ የሚለው ጥያቄ በጥቂት ቃላት ለመመለስ አስቸጋሪ ጥያቄ ነው፡፡ እንደፈለግነው ያልተለወጠውን የህይወታችን ...
Monday, February 28, 2022
Sunday, February 27, 2022
Tuesday, February 22, 2022
Friday, February 18, 2022
Sunday, February 13, 2022
የፍቅር ምንጭ
ስለ ፍቅር ብዙ ይዘከራል ይወራል፡፡
ሁሉም
ሰው ይህ የሚዘመርለትንና የሚሰበክለትን ፍቅር ማወቅ ፣ መኖር እና ማጣጣም ይፈልጋል፡፡ ነገር ግን ወደ ተግባር ሲመጣ ፍቅር በተግባር
ሊተረጎም የማይችል ረቂቅ ነገር ብቻ ይሆንበታል፡፡
ሰው
ደግሞ እውነተኛውን ፍቅርን ካልተረዳ ተመሳሳዩን ምኞትን እንደፍቅር ይዞት ባነሰ ነገር ረክቶ ይኖራል፡፡
ፍቅር
ግን ምኞት አይደለም፡፡ ፍቅር ስሜት አይደለም፡፡ ፍቅር ከፍ ያለ የህይወት ደረጃ ነው፡፡
ስለፍቅር
የሚናገሩትን መፅሃፍት በማንበብ ፍቅር አይመጣም፡፡ ፍቅር ከሰው አይመጣም፡፡ ሰው ራሱ ፍቅርን የተራበ እና ፍቅር የሚያስፈልገው
ፍጥረት ስለሆነ ፍቅርን በራሱ ሊሰጥ አይችልም፡፡
ፍቅር
የሚመጣው ፍቅር ከሆነው ከእግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
እግዚአብሔር
ፍቅር ነው፥ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል። 1ኛ ዮሐንስ 4፡16
ፍቅርን
ሊያውቅ በፍቅር ሊኖር የሚችለው በእግዚአብሄር የሚኖር ሰው እግዚአብሄርም በእርሱ የሚኖርበት ሰው ብቻ ነው፡፡
ሰው
ፍቅርን ከእግዚአብሄር ካላገኘ ምኞትን እንጂ ፍቅርን በፍፁም ሊያውቀው አይችልም፡፡
ሰው
ከእግዚአብሄር ፍቅርን ካልተቀበለ ፍቅርን ተቀብሎ አያውቅም፡፡ ሰው በእግዚአብሄር ፍቅር ጉልበት ካላገኘ በእውነተኛ ፍቅር ሌላውን
የሚወድበት አቅም አይኖረውም፡፡
ሰው
ምክኒያታዊ ያልሆነውን እውነተኛውን ፍቅርን መማር የሚችለው ፍቅር ከሆነው ከእግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
የእግዚአብሄርን
ፍቅር የቀመሰ ሰው ብቻ እውነተኛውን ፍቅር ያውቃል፡፡
የእግዚአብሄርን
ፍቅር የቀመሰ ሰው ብቻ የተቀበለውን ፍቅር ለሌላው መስጠት ይችላል፡፡
በተሰጠንም
በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን ስለ ፈሰሰ ተስፋ አያሳፍርም። ሮሜ 5፡5
በእግዚአብሄር
ፍቅር የረካ ሰው ብቻ ሌላውን ሰው በፍቅር ሊያረካ ይችላል፡፡
ሰው
የእግዚአብሄርን ፍቅር በተቀበለ መጠን የእንካ በእንካ ያልሆነውን ፍቅር ለሌላው መስጠት ይችላል፡፡
Abiy Wakuma Dinsa አቢይ ዋቁማ
ዲንሳ
ለተጨማሪ
ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
ለቪዲዮ
መልእክቶች
https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ
#ጌታ #እምነት #ፍቅር #ስር #መሰረት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #ቸርነት #ትግስት #ከቅዱሳንሁሉጋር #መታበይ #መመካት #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ