I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
የጥበብ መጀመሪያ እግዚአብሔርን መፍራት ነው፤ ሰነፎች ግን ጥበብንና ተግሣጽን ይንቃሉ። ምሳሌ 1፡7 እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው ለራሱ ክብር ነው ፡፡ ሰው ለእግዚአብሄር ፈጣሪነትና ባለቤትነት እውቅና መስጠቱ በጣም ...
-
ፆም በመንፈሳዊ ህይወታችን ውስጥ ትልቅ ስፍራ አለው፡፡ ፆም ለህይወታችን የሚጠቅመውን ነገሮች ከእግዚአብሄ ቃል እንመልከት 1. ስጋ ያለልክ እንዳይጠግብ ይጠቅማል ፆም እግዚአብሄርን የማይፈልገው የወ...
-
ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜ እላለሁ፥ ደስ ይበላችሁ። ፊልጵስዩስ 4፡4 እኛ በኢየሱስ አዳኝነት ላመንንና ክርስቶስን ለምንከተል ሁላችን ደስ መሰኘት የተሰጠን ስጦታ ነው፡፡ ደስ ላለመሰኘት ምክኒያት የ...
-
የአእምሮ እውቀት ብቻ በራሱ መጥፎ ባይሆንም እንደመገለጥ እውቀት የሰውን ህይወት አይለውጥም፡፡ ህይወታችን በመገለጥ እውቀት ካልተለወጠ ደግሞ እግዚአብሄር በምድር ሰርተን አንድናልፍ ያዘጋጀልንን መልካሙን ስራ ፈፅመን ...
-
ስለሰው ማንነት የእግዚአብሄር ቃል ምን እንደሚያስተምር መረዳታችን ስለፍጥረታችን እንድንረዳና ከአፈጣጠራችን ጋር አብረን እንድንፈስ ያስችለናል፡፡ ስለሰው ማንነት የእግዚአብሄር ቃል የሚያስተምረውን መረዳታችን ሶስቱን የ...
-
እግዚአብሔር ይችል ነበር ስላልፈለገ ነው
-
ብዙ ጊዜ አመት ሲጠቀስ አብሮ ዓ.ም. ወይም አመተ ምህረት ተብሎ ይጠቀሳል፡፡ ይህ አመተ ምህረት የሚለው ቃል የሚያመለክተው ኢየሱስ ስለሃጢያታችን በመስቀል ላይ ሊሰቀል ከመጣበት ጊዜ ጀምሮ እስካሁን ያለውን ጊዜ ነው...
-
በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤ እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው። እግዚአብሔርን ፈልጉት፥ ትጸናላችሁም፤ ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ። 1ኛ ዜና 16፡10-11 መፅሃፍ ቅዱስ እግዚአብሄርን ስለመፈለግ ግልፅ ...
-
በምድር ላይ በህይወት ስኬታማ መሆን የማይፈልግ ሰው የለም፡፡ በተለይ ደግሞ በጋብቻው ስኬታማ መሆን የማይፈልግ ጤነኛ ሰው በአለም ላይ አይገኝም፡፡ ታዲያ እግዚአብሄር በትዳር ውስጥ ያስቀመጠውን ሙሉ በረከት ተጠቃሚ የምን...
Monday, February 28, 2022
Sunday, February 27, 2022
Tuesday, February 22, 2022
Friday, February 18, 2022
Sunday, February 13, 2022
የፍቅር ምንጭ
ስለ ፍቅር ብዙ ይዘከራል ይወራል፡፡
ሁሉም
ሰው ይህ የሚዘመርለትንና የሚሰበክለትን ፍቅር ማወቅ ፣ መኖር እና ማጣጣም ይፈልጋል፡፡ ነገር ግን ወደ ተግባር ሲመጣ ፍቅር በተግባር
ሊተረጎም የማይችል ረቂቅ ነገር ብቻ ይሆንበታል፡፡
ሰው
ደግሞ እውነተኛውን ፍቅርን ካልተረዳ ተመሳሳዩን ምኞትን እንደፍቅር ይዞት ባነሰ ነገር ረክቶ ይኖራል፡፡
ፍቅር
ግን ምኞት አይደለም፡፡ ፍቅር ስሜት አይደለም፡፡ ፍቅር ከፍ ያለ የህይወት ደረጃ ነው፡፡
ስለፍቅር
የሚናገሩትን መፅሃፍት በማንበብ ፍቅር አይመጣም፡፡ ፍቅር ከሰው አይመጣም፡፡ ሰው ራሱ ፍቅርን የተራበ እና ፍቅር የሚያስፈልገው
ፍጥረት ስለሆነ ፍቅርን በራሱ ሊሰጥ አይችልም፡፡
ፍቅር
የሚመጣው ፍቅር ከሆነው ከእግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
እግዚአብሔር
ፍቅር ነው፥ በፍቅርም የሚኖር በእግዚአብሔር ይኖራል እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል። 1ኛ ዮሐንስ 4፡16
ፍቅርን
ሊያውቅ በፍቅር ሊኖር የሚችለው በእግዚአብሄር የሚኖር ሰው እግዚአብሄርም በእርሱ የሚኖርበት ሰው ብቻ ነው፡፡
ሰው
ፍቅርን ከእግዚአብሄር ካላገኘ ምኞትን እንጂ ፍቅርን በፍፁም ሊያውቀው አይችልም፡፡
ሰው
ከእግዚአብሄር ፍቅርን ካልተቀበለ ፍቅርን ተቀብሎ አያውቅም፡፡ ሰው በእግዚአብሄር ፍቅር ጉልበት ካላገኘ በእውነተኛ ፍቅር ሌላውን
የሚወድበት አቅም አይኖረውም፡፡
ሰው
ምክኒያታዊ ያልሆነውን እውነተኛውን ፍቅርን መማር የሚችለው ፍቅር ከሆነው ከእግዚአብሄር ብቻ ነው፡፡
የእግዚአብሄርን
ፍቅር የቀመሰ ሰው ብቻ እውነተኛውን ፍቅር ያውቃል፡፡
የእግዚአብሄርን
ፍቅር የቀመሰ ሰው ብቻ የተቀበለውን ፍቅር ለሌላው መስጠት ይችላል፡፡
በተሰጠንም
በመንፈስ ቅዱስ የእግዚአብሔር ፍቅር በልባችን ስለ ፈሰሰ ተስፋ አያሳፍርም። ሮሜ 5፡5
በእግዚአብሄር
ፍቅር የረካ ሰው ብቻ ሌላውን ሰው በፍቅር ሊያረካ ይችላል፡፡
ሰው
የእግዚአብሄርን ፍቅር በተቀበለ መጠን የእንካ በእንካ ያልሆነውን ፍቅር ለሌላው መስጠት ይችላል፡፡
Abiy Wakuma Dinsa አቢይ ዋቁማ
ዲንሳ
ለተጨማሪ
ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
ለቪዲዮ
መልእክቶች
https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ
#ጌታ #እምነት #ፍቅር #ስር #መሰረት #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ልብ #ቸርነት #ትግስት #ከቅዱሳንሁሉጋር #መታበይ #መመካት #ደስታ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ