Popular Posts

Wednesday, July 29, 2026

በፊቱም ልባችንን እናሳርፋለን፥ እግዚአብሔር ከልባችን ይልቅ ታላቅ ነውና ሁሉንም ያውቃል። 1ኛዮሐንስ 3:19-20

 በፊቱም ልባችንን እናሳርፋለን፥ እግዚአብሔር ከልባችን ይልቅ ታላቅ ነውና ሁሉንም ያውቃል።

1ኛዮሐንስ 3:19-20 


Sunday, May 17, 2026

የምንሞትለት እንጂ የምንገድልለት አምላክም ሆነ ሀይማኖት የለንም!

 የምንሞትለት እንጂ የምንገድልለት አምላክም ሆነ ሀይማኖት የለንም! 


አምላክ ሀያል ነው የእኛ እርዳታ አይፈልግም። እንዲገድሉለት የሰውን እርዳታ የሚፈልግ ሀይማኖት እውነተኛ ሀይማኖት አይደለም። የሰውን እርዳታ የሚፈልግ ሀይማኖት ሀሰተኛ ሀይማኖት ነው። የሰውን እርዳታ የሚፈልግ ሀይማኖት ከሰይጣን ነው። 

ብዙ ሀይማኖቶች በምድር ላይ ቢኖሩም በአጠቃላይ ምድር ላይ ያሉት ሁለት አይነት ሀይማኖቶች ብቻ ናቸው። በምድር ላይ እውነተኛ እና ሀሰተኛ ሀይማኖት አለ። እግዚአብሔር አንድ ነው። ከአንድ በላይ እውነተኛ ሀይማኖት ሊኖር አይችልም። በአለም ላይ ከአንድ በላይ  ሀሰተኛ ሀይማኖት ሊኖር ግን ይችላል። 

ታዲያ ሀይማኖት መያዙ ሳይሆን እውነተኛውን አምላክ መያዛችንን እርግጠኛ እንሁን። እኔን በተመለከተ ፍለጋ አቁሜያለው እውነተኛውን አምላክ አግኝቻለሁ።

እውነተኛ አምላክ ብቻ የሆንህ አንተን የላክኸውንም ኢየሱስ ክርስቶስን ያውቁ ዘንድ ይህች የዘላለም ሕይወት ናት። ዮሐንስ 17:3 ሁሉም ሀይማኖት ወደ አንድ ፈጣሪ ያደርሳል የሚሉ በሰይጣን የተታለሉ ናቸው። 

ኢየሱስም አለው፡— እኔ መንገድና እውነት ሕይወትም ነኝ፤ በእኔ በቀር ወደ አብ የሚመጣ የለም። ዮሐንስ 14:6 

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa 

Sunday, April 12, 2026

ከእርሱ ጋር አስነሣን !



ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2፣6 7

ክርስቶስ ወደ ምድር የመጣው ስለእኛ ነው። ክርስቶስ ወደ ምድር የመጣው እኛ በሃጢያታችን ምክኒያት ቅዱስ ከሆነው ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላላም እንዳንለያይ ነው።

ሞት በሰው በኩል ስለ መጣ ትንሣኤ ሙታን በሰው በኩል ሆኖአልና። ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉና። 1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15፣21 22

ክርስቶስ ኢየሱስ የሞተው እኛ በሃጢያታችን መሞት የነበረበንን ሞት ነው። ክርስቶስ የሞተው በእኛ ምትክ ነው። ክርስቶስ የሞተው ለእኛ ነው።

በመጀመሪያ ሰው የተፈጠረው ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላላም እንዲኖር ነበር። በእግዚአብሔር የተፈጠረው ሃጢያትን የማያውቅ  ፍጹም ሰው ነበር።

ሰው ከእግዚአብሔር የተለየው ሃጢያት በሰራ ጊዜ ነበር።

እግዚአብሔር አምላክም ሰውን እንዲህ ብሎ አዘዘው፦ ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ፤ ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና። ዘፍጥረት 2፣16  17

ክርስቶስ የመጣው እኛ ወደፊት እንዳንሞት ከእግዚአብሔርም ጋር ለዘላላም እንዳንለያይ ነው።

ክርስቶስ ሃጢያት ያልተገኘበት ፍጹም ነው። ክርስቶስ መሞት አይገባውም  ነበር። ክርስቶስ የሞተው እኛ ሞት ሰለሚገባን ነበር። ክርስቶስ የሞተው እኛን ከሞት ሊያስነሳን በእኛ ምትክ ነው።  

ክርስቶስ የሞተው ለእኛ ትንሳኤን ሊሰጠን ነው።

እኛ ከክርስቶስ ጋር አብረነው ካልተነሳን ክርስቶስ በከንቱ ሞተ።

የክርስቶስ ሞትና ትንሳኤ "ከእለታት አንድ ቀን ክርስቶስ ከሞት ተነሳ" ብለን ብቻ የምናስታውሰው የክርስቶስ ታሪክ አይደለም። የክርስቶስ ትንሳኤ የእኛም ከሙታን የመነሳት ልምምድ ነው። በክርስቶስ ሞትና ተንሳኤ የምናምን ሁላችን ከሞት ተነስተናል።

ከወደደን ከትልቅ ፍቅሩ የተነሣ በበደላችን ሙታን እንኳ በሆንን ጊዜ ከክርስቶስ ጋር ሕይወት ሰጠን፥ በጸጋ ድናችኋልና፥ በሚመጡ ዘመናትም በክርስቶስ ኢየሱስ ለእኛ ባለው ቸርነት ከሁሉ የሚበልጠውን የጸጋውን ባለ ጠግነት ያሳይ ዘንድ፥ ከእርሱ ጋር አስነሣን በክርስቶስ ኢየሱስም በሰማያዊ ስፍራ ከእርሱ ጋር አስቀመጠን። ወደ ኤፌሶን ሰዎች 2፣5-7

የትንሳኤ በአል የክርስቶስ ብቻ ሳይሆን የእኛም የትንሳኤ በአል ነው።

መልካም የትንሳኤ በአል

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

Friday, November 28, 2025

የብልጽግና ወንጌል ምሥጢር ሲገለጥ


የብልጽግና ወንጌል ምሥጢር ሲገለጥ  

በወንጌል አላፍርምና፤ አስቀድሞ ለአይሁዳዊ ደግሞም ለግሪክ ሰው፥ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔር ኃይል ለማዳን ነውና። ወደ ሮሜ ሰዎች 1፡16

ወንጌል በሃጢያታቸው ምክኒያት  ለዘላለም ከእግዚአብሔር የተለያዩትን የሰው ልጆች  ከእግዚአብሔር ጋር ለዘላለም እንዲኖሩ የሚያስችል ታላቅ የምስራች ነው። 

አሁን ግን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ መገለጥ ታይቶአል። እርሱ ሞትን ሽሮአልና እኔ ሰባኪና ሐዋርያ አሕዛብንም አስተማሪ እንድሆን በተሾምሁበት በወንጌል ሕይወትንና አለመጥፋትን ወደ ብርሃን አውጥቶአል። 2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 1:10-11

ወንጌል ጠላቶች የነበሩትን የሰው ልጆች በማስታረቅ የእግዚአብሔር ወንድና ሴት ልጆች አድርጎ መቀበል የሚያስችል ታላቅ የምስራች ነው።

ለተቀበሉት ሁሉ ግን፥ በስሙ ለሚያምኑት ለእነርሱ የእግዚአብሔር ልጆች ይሆኑ ዘንድ ሥልጣንን ሰጣቸው፤ የዮሃንስ ወንጌል 1:12

ወንጌል በሃጢያት ምክኒያት ከሰይጣን የባርነት እስራት ወስጥ ሲሰቃዩ የነበሩትን የሰው ልጆች በሰይጣን ላይ ስልጣን የሚሰጥ የእግዚአብሔር ታላቅ የማዳኛ ሃይል ነው፡፡

እርሱ ደግሞ በሞት ላይ ሥልጣን ያለውን በሞት እንዲሽር፥ ይኸውም ዲያብሎስ ነው፥ በሕይወታቸውም ሁሉ ስለ ሞት ፍርሃት በባርነት ይታሰሩ የነበሩትን ሁሉ ነጻ እንዲያወጣ፥ በሥጋና በደም እንዲሁ ተካፈለ። ወደ ዕብራውያን 2:14

#የብልጽግናወንጌል #ወንጌል #ኢየሱስ #የምስራች #እግዚአብሔር #የበለጸገ #መልካምዜና

Tuesday, January 28, 2025

Name it claim it Take it!

 



Name it claim it Take it!

“So Jesus answered and said to them, “Have faith in God. For assuredly, I say to you, whoever says to this mountain, ‘Be removed and be cast into the sea,’ and does not doubt in his heart, but believes that those things he says will be done, he will have whatever he says.”

‭‭Mark‬ ‭11‬:‭22‬-‭23‬ ‭NKJV‬‬

Jesus taught that we can speak to our mountains and have them removed. Jesus encouraged us to believe in God for the removal of our mountain by the word of our mouth.

Whoever believes in God will identify his need, look for a solution from the word, call it to be changed, and have the situation changed.

We look for the word to see the will of God for our lives. 

We have to believe God for it. Faith comes by hearing, and it comes by hearing the word of God. 

“So then faith comes by hearing, and hearing by the word of God.”

‭‭Romans‬ ‭10‬:‭17‬ ‭NKJV‬‬

Faith comes as soon as we know the will of God for our lives.

Once we know the will, we don’t stop thinking it will go away by itself.  We have actively claimed the desired result. Our confession must be aligned with our faith in our heart. We can't just believe and not confess thinking the work is done.

Once we confess what we believe from the word of God, we will have it.

It may take a while to manifest in the physical world, but in the spiritual, we have it already. We have to claim what we know the will of God for our lives is; we have to confess and call it into existence. And we will have it.

Name it claim it Take it!

Abiy Wakuma Dinsa

Thursday, January 2, 2025

ጸሎት እንዲመለስ የሚያደርገው

 

ጸሎት ከእግዚአብሄር ጋር መነጋገር ነው። ጸሎት ሊደረግ የሚችለው ከእግዚአብሄር ጋር በመግባባት ብቻ ነው። ጸሎት የሚሰምረው እንደ እግዚአብሄር አሳብ ስንጸልይ ብቻ ነው።

በአጠቃላይ ለእግዚአብሄር ያለን አመለካከት የጸሎታችንን ውጤታማነት ይወስናል።

ጸሎት ፍሬያማ የሚሆነው ለእግዚአብሄር የአምላክነት ስልጣን እውቅና በሰጠን መጠን ብቻ ነው። ጸሎት የሚሰምረው ከምስጋና ልብ ሲወጣ ብቻ ነው።

ሁልጊዜ ደስ ይበላችሁ፤ ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና። 1ኛ ወደ ተሰሎንቄ ሰዎች 5፡17-18

ወደ እግዚአብሄር በጸሎት የመቅረብ አንደኛው ደንብ ወይም አሰራር ምስጋና ነው።

ልመናና ጸሎት ምልጃም መቅረብ ያለበት በምስጋና ብቻ ነው።

እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ። 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2:1-2

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ  Abiy Wakuma Dinsa        

#እግዚአብሔርንመምሰል #ኢየሱስ #ጌታ #ምልጃ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ምስጋና #እምነት #አበሻ #አማርኛ #ሰላም #ደስታ #አዲስአመት #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ኢትዮጲያ #ፀሎት #ሀበሻ #ምስጋና


Tuesday, December 24, 2024

Dhalachuun Yesus Raawwii Raajichaa Ture


Kanaafis Waaqayyo ofii isaatii milikkita isiniif in kenna; kunoo, durbi in ulfoofti, ilmas in deessi, maqaa isaas Amaanu'el jettee in moggaafti; Amaanu'el jechuunis Waaqayyo nuu wajjin jira jechuu dha. Macaafa Isaayaas Raajichaa 7:14

Macaafa Qulqulluu keessatti raajichi Isaayaas Yesus dhalachuu isaa waggaa 700 dura waa’ee dhalachuu Yesus raajii dubbateera. Raajichi durbi ulfooftee ilma akka deesse dubbateera. Raajii keessatti maqaan mucaa dhalatu Ami'el akka ta'u dubbatameera. Hiikni maqaa Amaanu'eel nu waliin Waaqayyodha.

Raajichi kan raawwatame dubroo Maariyaam irraa Yesuus dhalachuu isaati.

Kun hundinuu inni Waaqayyo gooftaan afaan raajichaatiin dubbate akka raawwatamuuf ta'e. Innoo, Kunoo durbi in ulfoofti ilmas in deessi, maqaa isaas Amaanu'el jedhanii in moggaasu jedhe; Amaanu'el jechuun Waaqayyo nuu wajjin jira jechuu dha. Wangeela Maatewos 1:22-23

Waaqayyo nama kan uume akka isa waliin jiraachuu fi waldaa ta’uuf.

Kana booddee Waaqayyo, Kottaa! Akka bifa keenyaatti, akka fakkaattii keenyaattis nama in umnaa! Isaan qurxummii galaanaa irratti, simbiraa fi allaattii qilleensa keessa balali'an irratti, horii qe'ee irratti, bineensa lafaa hundumaa irratti, munyuuqaa lafa irra munyuuqu hundumaa irrattis mootummaa haa qabaatan! jedhe. Egaa Waaqayyo akka bifa isaatti nama uume, akka bifa Waaqayyootti isa uume; dhiiraa fi dubartii isaan uume;. Seera Uumamaa 1:26-27

Garuu Waaqayyoof ajajamuu diduudhaan namni guutummaatti Waaqayyo irraa adda ba’e.

Yommus Waaqayyo gooftaan namicha abboomee, Ija mukkeetii iddoo dhaabaa kana keessa jiran hundumaa irraa in nyaatta; ija mukicha nyaatanii hamaa fi gaarii ittiin beekan sana irraa garuu hin nyaatin! Gaafa isa irraa nyaatte garuu dhuguma in duuta jedhe. Seera Uumamaa 2:16-17

Iyyesuus ilmi Waaqayyoo sababa cubbuu keenyaaf karaa Dubroo Maariyaam gara lafaa dhufe.

Kun hundinuu inni Waaqayyo gooftaan afaan raajichaatiin dubbate akka raawwatamuuf ta'e. Innoo, Kunoo durbi in ulfoofti ilmas in deessi, maqaa isaas Amaanu'el jedhanii in moggaasu jedhe; Amaanu'el jechuun Waaqayyo nuu wajjin jira jechuu dha. WANGEELA MAATEWOS 1፡22-23

Abiy Wakuma Dinsa

#Cal'isaa #Cafaan #Kadhannaa #Waaqayyoo #Yesuus #Kadhannaa #Gooftaa #Waldaa #Lallaba #Fayyina #MacaafaQulqulluu #Qulqulluu #Faarfannaa #Amantii #oromo #Oromiffa #oromia #Oromiyaa #Nagaa #Gammachuu #Abiy #Abiywakuma #Abiywakumadinsa #Dubbachuu # Ethiopia #siyaasa #mootummaa

Monday, December 16, 2024

የኢየሱስ መወለድ የትንቢቱ መፈፀም ነበር

 

ስለዚህ ጌታ ራሱ ምልክት ይሰጣችኋል፤ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች፥ ወንድ ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ብላ ትጠራዋለች። ትንቢተ ኢሳይያስ 7፡14

በመጽሃፍ ቅዱስ ነቢዩ ኢሳያስ ስለ ኢየሱስ መወለድ ትንቢትን የተናገረው ኢየሱስ ከመወለዱ ከ700 አመት በፊት ነበር። ትንቢቱም ድንግል እንደምትጸንስ ወንድ ልጅም እንደምትወልድ ተናግሮ ነበር። የሚወለደው ልጅ ስም አማኤል እንደሚባል በትንቢቱ ተነግሮ ነበር። አማኑኤል የሚለው ስም ትርጉም እግዚአብሄር ከእኛ ጋር ማለት ነው።

ትንቢቱ በኢየሱስ ከድንግል ማርያም መወለድ ተፈጸመ። 

በነቢይ ከጌታ ዘንድ፦ እነሆ፥ ድንግል ትፀንሳለች ልጅም ትወልዳለች፥ ስሙንም አማኑኤል ይሉታል የተባለው ይፈጸም ዘንድ ይህ ሁሉ ሆኖአል፥ ትርጓሜውም፦ እግዚአብሔር ከእኛ ጋር የሚል ነው። የማቴዎስ ወንጌል 1፡22-23 

እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው ከእርሱ ጋር እንዲኖር እና ህብረት እንዲያደርግ ነበር። 

እግዚአብሔርም አለ፦ ሰውን በመልካችን እንደ ምሳሌአችን እንፍጠር፤ የባሕር ዓሦችንና የሰማይ ወፎችን፥ እንስሳትንና ምድርን ሁሉ፥ በምድር ላይ የሚንቀሳቀሱትንም ሁሉ ይግዙ። እግዚአብሔርም ሰውን በመልኩ ፈጠረ፤ በእግዚአብሔር መልክ ፈጠረው፤ ወንድና ሴት አድርጎ ፈጠራቸው። ኦሪት ዘፍጥረት 2፡26-27

ነገር ግን እግዚአብሄርን ባለመታዘዙ ሰው ከእግዚአብሄር ፍጹም ተለያይቶ ነበር።

እግዚአብሔር አምላክም ሰውን እንዲህ ብሎ አዘዘው፦ ከገነት ዛፍ ሁሉ ትበላለህ፤ ነገር ግን መልካምንና ክፉን ከሚያስታውቀው ዛፍ አትብላ፤ ከእርሱ በበላህ ቀን ሞትን ትሞታለህና። ኦሪት ዘፍጥረት 2፡16-17

የእግዚአብሄር ልጅ የሆነው ኢየሱስ በድንግል ማርያም በኩል ወደምድር የመጣው በሃጢያታችን ምክኒያት ነው።

አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa

#ፀሎት #ፈቃዱ #መልስ #ኢየሱስ #ጌታ #ጋብቻ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ሚስት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ክሪስማስ #እምነት #ወንድ #ፍቅር #ትዳር #ሰላም #ልደት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #ገና

Sunday, December 15, 2024

Dhalachuun Yesus Raawwii Raajichaa Ture



 Dhalachuun Yesus Raawwii Raajichaa Ture

Kanaafis Waaqayyo ofii isaatii milikkita isiniif in kenna; kunoo, durbi in ulfoofti, ilmas in deessi, maqaa isaas Amaanu'el jettee in moggaafti; Amaanu'el jechuunis Waaqayyo nuu wajjin jira jechuu dha. Macaafa Isaayaas Raajichaa 7:14

Macaafa Qulqulluu keessatti raajichi Isaayaas Yesus dhalachuu isaa waggaa 700 dura waa’ee dhalachuu Yesus raajii dubbateera. Raajichi durbi ulfooftee ilma akka deesse dubbateera. Raajii keessatti maqaan mucaa dhalatu Ami'el akka ta'u dubbatameera. Hiikni maqaa Amaanu'eel nu waliin Waaqayyodha.

Raajichi kan raawwatame dubroo Maariyaam irraa Yesuus dhalachuu isaati.

Kun hundinuu inni Waaqayyo gooftaan afaan raajichaatiin dubbate akka raawwatamuuf ta'e. Innoo, Kunoo durbi in ulfoofti ilmas in deessi, maqaa isaas Amaanu'el jedhanii in moggaasu jedhe; Amaanu'el jechuun Waaqayyo nuu wajjin jira jechuu dha. Wangeela Maatewos 1:22-23

Waaqayyo nama kan uume akka isa waliin jiraachuu fi waldaa ta’uuf.

Kana booddee Waaqayyo, Kottaa! Akka bifa keenyaatti, akka fakkaattii keenyaattis nama in umnaa! Isaan qurxummii galaanaa irratti, simbiraa fi allaattii qilleensa keessa balali'an irratti, horii qe'ee irratti, bineensa lafaa hundumaa irratti, munyuuqaa lafa irra munyuuqu hundumaa irrattis mootummaa haa qabaatan! jedhe. Egaa Waaqayyo akka bifa isaatti nama uume, akka bifa Waaqayyootti isa uume; dhiiraa fi dubartii isaan uume;. Seera Uumamaa 1:26-27

Garuu Waaqayyoof ajajamuu diduudhaan namni guutummaatti Waaqayyo irraa adda ba’e.

Yommus Waaqayyo gooftaan namicha abboomee, Ija mukkeetii iddoo dhaabaa kana keessa jiran hundumaa irraa in nyaatta; ija mukicha nyaatanii hamaa fi gaarii ittiin beekan sana irraa garuu hin nyaatin! Gaafa isa irraa nyaatte garuu dhuguma in duuta jedhe. Seera Uumamaa 2:16-17

Iyyesuus ilmi Waaqayyoo sababa cubbuu keenyaaf karaa Dubroo Maariyaam gara lafaa dhufe.

Kun hundinuu inni Waaqayyo gooftaan afaan raajichaatiin dubbate akka raawwatamuuf ta'e. Innoo, Kunoo durbi in ulfoofti ilmas in deessi, maqaa isaas Amaanu'el jedhanii in moggaasu jedhe; Amaanu'el jechuun Waaqayyo nuu wajjin jira jechuu dha. WANGEELA MAATEWOS 1፡22-23

Abiy Wakuma Dinsa

#Cal'isaa #Cafaan #Kadhannaa #Waaqayyoo #Yesuus #Kadhannaa #Gooftaa #Waldaa #Lallaba #Fayyina #MacaafaQulqulluu #Qulqulluu #Faarfannaa #Amantii #oromo #Oromiffa #oromia #Oromiyaa #Nagaa #Gammachuu #Abiy #Abiywakuma #Abiywakumadinsa #Dubbachuu # Ethiopia #siyaasa #mootummaa

Thursday, November 7, 2024

የክህነት ህይወት አቢይ ዋቁማ ዲንሳ The Life of Priesthood Abiy Wakuma Dinsa


የክህነት ህይወት አቢይ ዋቁማ ዲንሳ The Life of Priesthood Abiy Wakuma Dinsa  

Wednesday, November 6, 2024

ያላችሁም ይብቃችሁ! አካሄዳችሁ ገንዘብን ያለ መውደድ ይሁን፥ ያላችሁም ይብቃችሁ፤ እርሱ ራሱ። አልለቅህም ከቶም አልተውህም ብሎአልና፤ ወደ ዕብራውያን 13:5 ሰዎች ጥፋት የሚያጠፉት አሁን ጥፋት ላጥፋ ብለው አቅደው አይደለም። አብዛኛውን ጊዜ ሰዎች ጥፋት የሚያጠፉት በሀሳባቸው ተታለው ነው። ሰዎች ሁሌ የተሻለ የበለጠ ነገር ይፈልጋሉ። ደግሞም ብዙ ጊዜ የሌላቸው ነገር ሁሉ የተሻለ የበለጠ ነገር ይመስላቸዋል። ታዲያ ሰዎች በተለይ የተሻለ ደስታን ፈልገው የተሳሳተ እርምጃ በመውሰዳቸው ምክንያት የማይወጡበት ሱስ ውስጥ ይገባሉ። ያለኝ ደስታ አይበቃኝም ብለው በትእቢት በማሰብ ደስታን በተሳሳተ ቦታ ሲፈልጉት የማይወጡት እስራት ውስጥ ወድቀው ራሳቸውን ያገኛሉ። ከነበራቸው ደስታ በላይ ያስፈልጋቸው እንዳልነበር እና የናቁት ደስታ ይበቃቸው እንደነበረ የሚረዱት ከረፈደ በኋላ ነው። እመኑኝ አሁን ከናቃችሁት የደስታ ደረጃ በላይ ያስፈልጋችሁ እንዳልነበረ የምትረዱት አሁን ያላችሁን ደስታ በንቀት ያጣችሁት ቀን ነው። አሁን እናንተ ያላችሁም ደስታ ይብቃችሁ። አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa #ፀሎት #ፈቃዱ #መልስ #ኢየሱስ #ጌታ #ጋብቻ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ሚስት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ባል #እምነት #ወንድ #ፍቅር #ትዳር #ሰላም #ሴት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

 

ያላችሁም ይብቃችሁ!


አካሄዳችሁ ገንዘብን ያለ መውደድ ይሁን፥ ያላችሁም ይብቃችሁ፤ እርሱ ራሱ። አልለቅህም ከቶም አልተውህምብሎአልና፤ ወደ ዕብራውያን 13:5  


ሰዎች ጥፋት የሚያጠፉት አሁን ጥፋት ላጥፋ ብለው አቅደው አይደለም። አብዛኛውን ጊዜ ሰዎች ጥፋትየሚያጠፉት በሀሳባቸው ተታለው ነው። 


ሰዎች ሁሌ የተሻለ የበለጠ ነገር ይፈልጋሉ። ደግሞም ብዙ ጊዜ የሌላቸው ነገር ሁሉ የተሻለ የበለጠ ነገርይመስላቸዋል። 


ታዲያ ሰዎች በተለይ የተሻለ ደስታን ፈልገው የተሳሳተ እርምጃ በመውሰዳቸው ምክንያት የማይወጡበት ሱስውስጥ ይገባሉ። ያለኝ ደስታ አይበቃኝም ብለው በትእቢት በማሰብ ደስታን በተሳሳተ ቦታ ሲፈልጉት የማይወጡትእስራት ውስጥ ወድቀው ራሳቸውን ያገኛሉ። 


ከነበራቸው ደስታ በላይ ያስፈልጋቸው እንዳልነበር እና የናቁት ደስታ ይበቃቸው እንደነበረ የሚረዱት ከረፈደ በኋላነው። 


እመኑኝ አሁን ከናቃችሁት የደስታ ደረጃ በላይ ያስፈልጋችሁ እንዳልነበረ የምትረዱት አሁን ያላችሁን ደስታበንቀት ያጣችሁት ቀን ነው። 


አሁን እናንተ ያላችሁም ደስታ ይብቃችሁ።  


አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa


#ፀሎት #ፈቃዱ #መልስ #ኢየሱስ #ጌታ #ጋብቻ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ሚስት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ባል#እምነት #ወንድ #ፍቅር #ትዳር #ሰላም #ሴት #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር#ፅናት #ትግስት #መሪ

Wednesday, October 30, 2024

የአሜሪካ የፕሬዝዳንታዊነት ምርጫ

የአሜሪካ የፕሬዝዳንታዊነት ምርጫ የአሜሪካዊያንንም ይሁን ይነስም ይብዛም በአጠቃላይ የአለምን ህዝብ ትኩረት የሳበ ርእስ ነው። 
እንደ ክርስትያን በፖለቲካ ምርጫ መሳተፍ ምንም የማይወጣበት ትክክል ነገር ቢሆንም በሪፐብሊካንም ይሁን በዲሞክራት ላይ ያን ያህን ልባችንን መጣል እና ተስፋ ማድረግ እንደማይገባ ማስታወስ አለብን። 
ፖለቲከኞች በፖለቲካ ፖሊሲ ወይም መመሪያቸው የሚለያዩ ቢሆኑም ሪፐብሊካንም ይሁን ዲሞክራት ቢያሸንፍ እንደው ያን ያህል ስር ነቀል ልዩነት የሚያመጣ ነገር ያመጣል ብሎ መጠበቅ ሞኝነት ነው። 
እንደ ክርስትያን በምርጫ ካርዳችን ከምናመጣው ልዩነት በላይ ማንም ይሁን ማን ለተመርጠው እና በስልጣን ላይ ላለው መንግስት  እለት ተእለት ለነገስታት እና ለመኳንንት መጸለይ ይበልጥ በዘላቂነት ልዩነት ያመጣል። 
እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ በፊት እመክራለሁ። 1ኛ ወደ ጢሞቴዎስ 2፡1-2
እኛ ራሳችን ፖለቲከኞች ብንሆን እንኳን በምርጫ ቅስቀሳም ቢሆን በምርጫ ካርዳችን ከምናመጣው ልዩነት ይልቅ በጸሎታችን የምናመጣው ልዩነት እጅግ ይበልጣል። ሪፕብሊካን ይሁን ዲሞክራት ከሁሉም በላይ የእናንተን ልመናና ጸሎት ምልጃ ይፈልጋል። 
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
#ምርጫ #ጸሎት #ምልጃ #ምስጋና #ልመና #ክርስትያን #ፖለቲካ 


 

በቃልኪዳን መነጽር ህይወታችን ማየት አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa ሬማ እምነት አገልግሎት በርሚንግሃም ቤተክርስትያን

 https://youtu.be/VhF0pSsp14I

በቃልኪዳን መነጽር ህይወታችን ማየት አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa ሬማ እምነት አገልግሎት በርሚንግሃም ቤተክርስትያን

Tuesday, October 29, 2024

ሀሎዊን ክፍል 2

 

ሃሎዊን Halloween የሚባለው በአል በኦክቶበር ወር መጨረሻ ላይ በተለያ መልኩ ይከበራልባብዛኛው ህዝብ ዘንድ እንደ አንድ ባህል የሚብረው ይህ የሃሎዊን በአል ሰዎች ቢገባቸውም ባይገባቸውም መንፈሳዊ እንደምታ የለውም ማለት ግን አይቻልም 

 ሊሰርቅ ሊያርድ ሊያጠፋ እንጂ ስለሌላ አይመጣም የተባለው ጠላት ዲያቢሎስ ባገኘው አጋጣሚ የሰዎችን ህይወት ይሰርቃል ያርዳል ያጠፋል 

ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣምእኔ ሕይወት እንዲሆንላቸው እንዲበዛላቸውም መጣሁየዮሐንስ ወንጌል 10፣10 

 

ሰይጣን በእግዚአብሄር ይፈጠር የእግዚ መላክ የነበር ሳጥናኤል ነበርሳጥናኤል ሰይጣን የሆነው እና እርሱን ከተከተሉት የወደቁት መላእክት ጋር ከእግዚአብ ፊት ወደ ምድር የተጣለው ትእቢት እንደ እግዚአብ ሊሆን ስለፈለገ ነበር 

 

መኖሪያቸውንም የተዉትን እንጂ የራሳቸውን አለቅነት ያልጠበቁትን መላእክት በዘላለም እስራት ከጨለማ በታች እስከ ታላቁ ቀን ፍርድ ድረስ ጠብቆአቸዋልየይሁዳ መልእክት 1:6 

 

ሰይጣን ዲያብሎስ የእሳት ባህር ቅጣት ተዘጋጅቶልታል 

 

እስክዚያ ግን ቻለውን ያህል ሰው አታልሎ ብዙ ሰዎችን ወደ እሳት ባህር ሄድ ይፈልጋልየእሳት ባህር ለሰው ያልተዘጋጀ ቢሆንም እግዚአብሄር በክርስቶስ ሱስ ውን ከሃጢያት የመዳኛ ንገድ ያልተቀበሉ ሁሉ ለሰይጣን እና ለመላእክቱ ወደተዘጋጀው የእሳት ባህር ይጣላሉ 

 

እግዚአብሄር በክርስቶስ ኢየሱስ ያዘጋጀውን ከሃጢያት የመዳኛ መንገድ የተቀብሉ ብቻ ከእግዚአብሄር ጋር ለዘላ አይለያዩም ለሰይጣን እና ለመላእክቱ ወደተዘጋጀው የእሳት ባህር አይጣሉ 

 

በዚያን ጊዜ በግራው ያሉትን ደግሞ ይላቸዋልእናንተ ርጉማንለሰይጣንና ለመላእክቱ ወደ ተዘጋጀ ወደ ዘላለም እሳት ከእኔ ሂዱየማቴዎስ ወንጌል 25:11 

 

 አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa  

#ሰይጣን #ሀሎዊን #ሃሎዊን #ጠላት #ዲያቢሎስ #አቢይዋቁማ #ኢየሱስጌታ #ኢየሱስ