I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ለተሳካ ህይወትና ለአገልግሎት ራእይ ወሳኝ ነገር ነው፡፡ ራእይ ከየት እንደመጣን ወዴት እንደምንሄድ ይጠቁመናል፡፡ አንዳንድ ሰዎች ራእይ ሊጨበጥ የማይችል ሃይማኖታዊ ሃሳብ ብቻ ይመስላቸዋል፡፡ ስለዚህ አንዳንድ ሰዎች...
-
ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱ...
-
የምድር መሠረቶች የእግዚአብሔር ናቸውና! ABIY WAKUMA DINSA BLOG · SATURDAY, 20 AUGUST 2016 ሰው በምድር ላይ እንዲበረክት አለመታበይ አለበት፡፡ ሰው በምድር ላይ ተቋቁሞ...
-
-
It isn’t only what we do in life that matters it is also why we do the things we do. Even our good activities should be checked as in w...
-
በእኔ ላይ ግን አንድ ነገር እንኳ አይሠለጥንብኝም። መብል ለሆድ ነው፥ ሆድም ለመብል ነው፤ እግዚአብሔር ግን ይህንም ያንም ያጠፋቸዋል። 1 ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6 ፡ 12-13 ...
-
እኛ በጌታ በኢየሱስ አዳኝነት አምነን የዳንን እና የእግዚአብሄር ልጆች የሆንን ሁላችን የአባታችንን እግዚአብሄርን ፍቅር ተካፍለናል፡፡ የእግዚአብሄር ፍቅር በልባችን ፈሷል፡፡ በተሰጠን...
-
Miracle Everyday God created us for a purpose. He is busy working in our lives. We are created for the supernatural. We see God working in ...
Tuesday, October 11, 2022
Sunday, October 2, 2022
ርህራሔ የሌለበት የኢሬቻ አስተያየት
Saturday, October 1, 2022
የአዲሱ ኪዳን ፀሎት ትኩረት
ክርስቶስ ስለሃጢያታችን በመስቀል ላይ ከሞተ እና በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ከተነሳ በኋላ የምንኖርበት ኪዳን በኢየሱስ የተደረገው አዲስ ኪዳን ነው፡፡
ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት በሃጢያታችን ምክኒያት
ከእግዚአብሄር ጋር ጠላቶች ነበርን፡፡ ኢየሱስ በመስቀል ላይ ስለሃጢያታችን በመሞት ከእግዚአብሄር ጋር አስታርቆናል፡፡ አሁን ከእግዚአብሔር
ጋር ሰላም ነን፡፡
ኢየሱስ በመስቀል ላይ በመሞት በብሉይ ኪዳን ለጥቂት
ለተመረጡ ሰዎች ይሰጥ የነበረውንም መንፈስ ቅዱስን እርሱን ለተቀበልን ለሁላችንም እንዲሰጠን እና መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን አንዲኖር
አስችሎናል፡፡
ከእግዚአብሄር ጋር ጥል በነበሩበትና በክርስቶስ
ደም ባልታረቁበት ጊዜ የሚፀለየውን ፀሎቶች በዚህ በአዲሱ ኪዳን ብንፀልይ ውጤታማ አንሆንም፡፡
በአዲሱ ኪዳን የተፀለየውን አንዱን ፀሎት ለምሳሌ
ብንወስድ ፀሎቱ የሚያተኩረው ክርስቶስ በመስቀል ላይ የሰራልንን ስራ በመረዳት ላይ ነው፡፡
የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ። ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤ ኤፌሶን 1፡17-19
ይህ አይነቱን ፀሎት ፍሬያማ የሚያደርገው በመስቀል
ላይ የተሰራውን ስራ እውቅና መስጠቱ ነው፡፡ እንዲሁም ይህን ተሰርቶ የተጠናቀቀውን ስራ በሚገባ እንድንረዳ አይናችን እንዲከፈት
እግዚአብሄርን መለመኑ ነው፡፡ እንደዚህ አይነቱ የአዲስ ኪዳን ፀሎት እግዚአብሄርን በማወቅ የጥበብ እና የመገለጥ መንፈስ እንዲሰጠን
ይጠይቃል፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma
Dinsa