I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
አንድነት ተመሳሳይነት አይደለም፡፡ አንድነት በአንድ ጣራ ስር መሰብሰብ አይደለም፡፡ አንድነት ተመሳሳይ ነገር ማሰብ እና ማድረግ አይደለም፡፡ አንድነት ተመሳሳይ ስጦታ መኖር አይደለም፡፡ አንድነትን በተመሳሳይነት መ...
-
እግዚአብሄር በመጀመሪያ የፈጠረን በጤንነት ነው፡፡ ከጥንት እግዚአብሄር ሙላትን ፣ ጤንነትን እና ብርታትን እንጂ በሽታንና ደዌን አልፈጠረም፡፡ በማንኛውም ምክኒያት ጤንነታችንን ብናጣና ብን...
-
አንደኛው የእግዚአብሄር ስም ፈዋሽ አምላክ የሚል ነው፡፡ እግዚአብሄር በመፈወስ ይታወቃል፡፡ እግዚአብሄር ሰዎችን ሙሉ በማድረግ ይታወቃል፡፡ ነፍሴ ሆይ፥ እግዚአብሔርን ባርኪ፥ ምስጋናውንም ሁሉ አትርሺ፤ ኃጢአ...
-
ክርስቶስ ስለሃጢያታችን ከቃሉ በመስቀል ላይ እንደሞተ ከቃሉ ስናይ ደህንነታችንን እንቀበላለን፡፡ እንዲሁም ኢየሱስ ስለሃጢያታችን መገረፉን ከልባችን ስንረዳ በሽታ በእኛ ላይ አቅም አይኖረውም፡፡ የሰው ፈውስ በመስቀል ...
-
አስቀድማችሁ ከፈሪሳውያን እርሾ ተጠበቁ! ክፍል 7 ባስተላለፋችሁትም ወግ የእግዚአብሔርን ቃል ትሽራላችሁ፤ እንደዚሁም ይህን የሚመስል ብዙ ነገር ታደርጋላችሁ። የማርቆስ ወንጌል 7፡13 ፈሪሳዊያን እንጅ ታጥቦ ስለ መብላይ...
-
ማሪያም ታማልዳለች ወይስ አታማልድም የሚለው ጥያቄ በኢትዮጲያ ውስጥ ብዙ ክርክርን ሲያስነሳ የቆየ ጥያቄ ነው፡፡ አንዳንዶች ማሪያም በምድር ላይ እያለች አማልዳለች ነገር ግን ከሞተች በኃላ ማማለድ አትችልም ብለው...
-
Love is patient, love is kind. It does not envy, it does not boast, it is not proud. It does not dishonor others, it is not self-seeking, ...
-
እንዲህ ሲል፦ በአንዲት ከተማ እግዚአብሔርን የማይፈራ ሰውንም የማያፍር አንድ ዳኛ ነበረ። በዚያችም ከተማ አንዲት መበለት ነበረች፥ ወደ እርሱም እየመጣች፦ ከባላጋራዬ ፍረድልኝ ትለ...
Wednesday, October 12, 2022
Sunday, October 2, 2022
ርህራሔ የሌለበት የኢሬቻ አስተያየት
የአዲሱ ኪዳን ፀሎት ትኩረት
ክርስቶስ ስለሃጢያታችን በመስቀል ላይ ከሞተ እና በሶስተኛው ቀን ሞትን ድል አድርጎ ከተነሳ በኋላ የምንኖርበት ኪዳን በኢየሱስ የተደረገው አዲስ ኪዳን ነው፡፡
ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት በሃጢያታችን ምክኒያት
ከእግዚአብሄር ጋር ጠላቶች ነበርን፡፡ ኢየሱስ በመስቀል ላይ ስለሃጢያታችን በመሞት ከእግዚአብሄር ጋር አስታርቆናል፡፡ አሁን ከእግዚአብሔር
ጋር ሰላም ነን፡፡
ኢየሱስ በመስቀል ላይ በመሞት በብሉይ ኪዳን ለጥቂት
ለተመረጡ ሰዎች ይሰጥ የነበረውንም መንፈስ ቅዱስን እርሱን ለተቀበልን ለሁላችንም እንዲሰጠን እና መንፈስ ቅዱስ በውስጣችን አንዲኖር
አስችሎናል፡፡
ከእግዚአብሄር ጋር ጥል በነበሩበትና በክርስቶስ
ደም ባልታረቁበት ጊዜ የሚፀለየውን ፀሎቶች በዚህ በአዲሱ ኪዳን ብንፀልይ ውጤታማ አንሆንም፡፡
በአዲሱ ኪዳን የተፀለየውን አንዱን ፀሎት ለምሳሌ
ብንወስድ ፀሎቱ የሚያተኩረው ክርስቶስ በመስቀል ላይ የሰራልንን ስራ በመረዳት ላይ ነው፡፡
የክብር አባት የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አምላክ እርሱን በማወቅ የጥበብንና የመገለጥን መንፈስ እንዲሰጣችሁ እለምናለሁ። ይህም የልባችሁ ዓይኖች ሲበሩ የመጥራቱ ተስፋ ምን እንዲሆን በቅዱሳንም ዘንድ ያለው የርስት ክብር ባለ ጠግነት ምን እንዲሆን ለምናምን ከሁሉ የሚበልጥ የኃይሉ ታላቅነት ምን እንዲሆን ታውቁ ዘንድ ነው፤ ኤፌሶን 1፡17-19
ይህ አይነቱን ፀሎት ፍሬያማ የሚያደርገው በመስቀል
ላይ የተሰራውን ስራ እውቅና መስጠቱ ነው፡፡ እንዲሁም ይህን ተሰርቶ የተጠናቀቀውን ስራ በሚገባ እንድንረዳ አይናችን እንዲከፈት
እግዚአብሄርን መለመኑ ነው፡፡ እንደዚህ አይነቱ የአዲስ ኪዳን ፀሎት እግዚአብሄርን በማወቅ የጥበብ እና የመገለጥ መንፈስ እንዲሰጠን
ይጠይቃል፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma
Dinsa
Saturday, October 1, 2022



