I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱ...
-
ፍቅር አስደናቂ ነው፡፡ በተለይ ፍቅር ሁሉን ያምናል የሚለውን ቃል ሳሰላስል ነበር ያመሸሁት፡፡ ይህን ቃል ሳሰላስል ጌታ የሰጠኝን መረዳት አብሬያችሁ ልካፈል ወደድኩ፡፡ ፍቅር ሁሉን ያምናል፡፡ 1ኛ ቆሮንጦስ ...
-
መጠበቅ ሁል ጊዜ ለስጋ አይመችም፡፡ ስጋ የሚፈልገው ሁሉ ነገር ወዲያው እንዲሆንለት ነው፡፡ ረጋ ብሎ ጠብቆ የሚሆንን ነገር የሚመርጠው ጥቅሙን የሚረዳ የበሰለ ሰው ብቻ ነው፡፡ ተፈጥሮአዊው ሰው ቢች...
-
በነጻነት ሕግ ፍርድን ይቀበሉ ዘንድ እንዳላቸው ሰዎች እንዲህ ተናገሩ፥ እንዲህም አድርጉ። የያዕቆብ መልእክት 2፡ 12 በክርስቶስ ከሃጢያት እስራትና ፍርድ ነፃ ወጥተናል፡፡ ነገር ግን ነፃነት የሚመጣ...
-
በሰዎችና በመላእክት ልሳን ብናገር ፍቅር ግን ከሌለኝ እንደሚጮኽ ናስ ወይም እንደሚንሽዋሽዋ ጸናጽል ሆኜአለሁ። ትንቢትም ቢኖረኝ ምሥጢርንም ሁሉና እውቀትን ሁሉ ባውቅ፥ ተራሮችንም እስካ...
-
በክርስትና ህይወት ዘመኔ ድንበርን እንደማለፍና ልክን እንዳለማወቅ የክርስቲያንን ሰላም የሚረብሽ ነገር አላየሁም፡፡ ክርስትና የእግዚአብሄርና የሰው ድርሻ ያለበት ስራ ነው፡፡ እግዚአብሄር የሚሰራው ነገር አለ፡፡ ሰው...
-
እናንተ ደግሞ እንደ ሕያዋን ድንጋዮች ሆናችሁ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ለእግዚአብሔር ደስ የሚያሰኝ መንፈሳዊ መሥዋዕትን ታቀርቡ ዘንድ ቅዱሳን ካህናት እንድትሆኑ መንፈሳዊ ቤት ለመሆን ተሠ...
-
Our lives should be lived with the intent of fulfilling God's purpose for us, rather than simply existing. That is the final conclusio...
-
ክርስቲያኖች ኢየሱስ ጌታ ነው በሚለው ንግግራቸው ይታወቃሉ፡፡ ኢየሱስ ጌታ ነው በሚለው የሶስት ቃላት አረፍተ ነገር ውስጥ እጅግ የተጠቀጠቁ ትርጉሞች ይገኙበታል፡፡ ኢየሱስ ጌታ ነው ሲባል 1. ኢየሱስ በሰማይ ...
-
ስለ ንፍታሌምም እንዲህ አለ፦ ንፍታሌም በሞገስ ጠግቦአል፥ የእግዚአብሔርንም በረከት ተሞልቶአል፤ ባሕሩንና ደቡቡን ይወርሳል። ኦሪት ዘዳግም 33፡23 እነሆ፥ የማታውቀውን ሕዝብ ትጠራለህ፥ የእ...
Tuesday, June 29, 2021
Tuesday, June 22, 2021
ለፀፀት እንቢ እንበል!
ፀፀት አንድ ሰው በሠራው ነገር ወይም አንድን ነገር ባለማድረጉ የሚሰማው የሐዘን ወይም የቁጭት ስሜት ነው፡፡
ህይወት በውሳኔ የተሞላ ነው፡፡ በህይወታችን በየደቂቃውና
በየሰከንዱ ቅድሚያ የሚሰጠውን ነገር በመለየት ሂደት ብዙ ውሳኔዎችን እንወስናለናን፡፡ በህይወታችን ትንሽ ከሚባለው ነገር ጀምሮ
ትልቅ እስከሚባለው ውሳኔ ድረስ አማራጮችን አመዛዝነን ውሳኔዎችን እንወስናለን፡፡
በየቀኑና በየደቂቃው አንድን ነገር ለማድረግ ወይም
ላለማድረግ መወሰን ተፈጥሮአዊ ግዴታ ነው፡፡ አንድን ነገር ለማድረግ በወሰንን በዚያው ቅፅበት ሌላውን አማራጭ ላለማድረግ እየወሰንን
ነው፡፡ አንድን ነገር ላለማድረግ በወሰንን ቅፅበት ሌላውን አማራጭ ለማድረግህ እየወሰንን ነው፡፡
ውሳኔ ስንወስን ያለንን እውቀት ፣ ማስተዋል እና
ጥበብ ሁሉ ተጠቅመን እንወስናለን፡፡ አብዛኛውን ጊዜ የምንወስነው ላለንበት ጊዜ እና ላለንበት ሁኔታ የተሻለውንና ትክክል የሆነውን
ውሳኔ ነው፡፡ ለነበርንበት ሁኔታ ከዚያ ከወሰነው ውሳኔ በላይ ልንወስን እንችልም ነበር፡፡
ታዲያ ችግሩ የሚመጣው የህይወት ተግዳሮት ሲደርስብን
አንድ ቀን የወሰንነውን ውሳኔ መጠራጠር ስንጀምር ነው፡፡
ልጆች ሆነን አደጋ ስለ ደረሰበት ልጅ ወላጆቻችን
ሲያወሩ እንሰማ ነበር፡፡ ታዲያ ልጁ አደጋ ሳይደርስበት በፊት የጠየቀው ጥያቄ ፣ የፈለገው ፍላጎት እና የለመንው ልመና ሁሉ ለፀፀት
ምክኒያት ሆኖ ሲቀርብ እንሰማ ነበር፡፡ ልጁ ሱቅ ከመላኩ በፊት እማዬ ርቦኛል ብሎ እናቱ ምሳ አልደረሰም ስትመጣ ትበላለህ ብላው
ከሄደ ምነው በሰጠሁትና በበላ ኖሮ ብላ ትፀፀታለች፡፡
ደግም እንፀፀት ካልን የማይፀፅት ነገር የለም፡፡
ለፀፀት ፊት ከሰጠነው በቁማችን ሊውጠን የሚችል ክፉ ሃይል ያለው ነገር ነው፡፡
የሰውን ህይወት ለመስረቅ ለማረድና ለማጥጭፋት
ፀፀተን የሚጠቀመው ሰይጣን ነው፡፡ ሰይጣን እኛን ለማሰቃየት ብዙ የህይወትን ተግዳሮት ያለፍንባቸውን ውሳኔዎች አይጠቀምባቸውም፡፡
በህይወታችን የወሰናቸውን አያሌ ውሳኔዎች እኛን ፀፀት ውስጥ ለመክተት ብዙ ጊዜ አይመቹትም፡፡
ነገር ግን የሰይጣን ብቸኛ አላማ መስረቅ ማረድና ማጥፋት ስለሆነ እንደ አጋጣሚ
ከውሳኔያችን በኋላ የተፈጠረውን ነገር ግን ከውሳኔያችን ጋር ምንም የማይገናኘውን ሁኔታ እያስታወሰ ሊያሰቃየን ይሞክራል፡፡ የሰይጣን
አላማ እኛን ዝቅ ዝቅ ማድረግህ ነው፡፡ የሰይጣን አላማ እኛን በፀፀት ሽባ እድርጎ ዛሬን እና ነገን ለእግዚአብሄር እንዳንኖር ማድረግ
ነው፡፡
እግዚአብሄር ይመራናል ያስጠንነቅናል እንጂ በፀፀት አያሰቃየንም፡፡
እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ኀዘን ጸጸት የሌለበትን፥ ወደ መዳንም የሚያደርሰውን
ንስሐ ያደርጋልና፤ የዓለም ኀዘን ግን ሞትን ያመጣል። 2ኛ ቆሮንቶስ 7፡10
አብዛኛውን ጊዜ የምንንፀፀትበት ነገር እግዚአብሄር የሌለበት ነገር ነው፡፡ የእግዚአብሄር
መንፈስ ወቀሳ የሚያበረታታ ፣ የተሻልን ሰዎች እንድንሆን የሚያደርግ እና የተሻለ አድርጎ የሚያስነሳ እና ተስፋ የሚሰጥ እንጂ ባለፈው
ህይወታችን ውስጥ በፀፀት በመኖር ዛሬን እና ወደፊታችንን እንድናባክነው የሚያደርግ አይደለም፡፡
ለፀፀት እንቢ እንበል!
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች
https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/
ለቪዲዮ መልእክቶች
https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ፀፀት #መካድ #መታለል #ታማኝነት #ክህደት #ንስሃ #ሃዘን #መመለስ #መሰደድ #ሃዋሪያዊ #መውደቅ #አለመመረጥ #ተቀባይነትማጣት #ዋጋአሰጣጥ #አእምሮ #ልብ #ኢየሱስ #ጌታ #መፅሃፍቅዱስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አምልኮ #እምነት #መከተል
Wednesday, June 9, 2021
መተቸት በጣም ቀላል ነው ፡፡ ሰዎች ሲተቹ እሰማለሁ እናም ስለ መሪዎቻችን እንደማይጸልዩ አውቃለሁ; ስለ ሌሎች በምንጸልይበት ጊዜ እነሱን ለመንቀፍ በጣም ተስማሚ አይደለንምና ፡፡ እኛ ክርስቲያኖች ግን ፖለቲካን ከክርስቶስ በፊት ማስቀደም የለብንም ፡፡ አንዳንድ ሰዎች ከመጠን በላይ በፖለቲካ አስተሳሰብ ውስጥ በመያዛቸው የተነሳ ጥሩ መንፈሳዊ ሰዎች መሆን አይችሉም ፡፡ ኬኔዝ ኢ ሀጊን የሚማልዱ ክርስትያኖች It's so easy to criticize. I hear people criticize and I know they are not praying for our leaders; for when we pray for others we are not so apt to criticize them. As Christians, however, we are not to put politics before Christ. Some people are so politically minded they are no good spiritually. Kenneth E Hagin The Interceding Christians
መተቸት
በጣም ቀላል ነው ፡፡ ሰዎች ሲተቹ እሰማለሁ እናም ስለ መሪዎቻችን እንደማይጸልዩ አውቃለሁ; ስለ ሌሎች በምንጸልይበት ጊዜ እነሱን ለመንቀፍ በጣም ተስማሚ አይደለንምና ፡፡
እኛ
ክርስቲያኖች ግን ፖለቲካን ከክርስቶስ በፊት ማስቀደም የለብንም ፡፡ አንዳንድ ሰዎች ከመጠን በላይ በፖለቲካ አስተሳሰብ ውስጥ በመያዛቸው የተነሳ ጥሩ መንፈሳዊ ሰዎች መሆን አይችሉም ፡፡ ኬኔዝ ኢ ሀጊን የሚማልዱ ክርስትያኖች
It's
so easy to criticize. I hear people criticize and I know they are not praying
for our leaders; for when we pray for others we are not so apt to criticize
them.






