I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
Name it claim it Take it! “So Jesus answered and said to them, “Have faith in God. For assuredly, I say to you, whoever says to this mount...
-
አንድ አረጋዊ በ ባሕር ዳርቻ መንገድ ላይ እየሄደ እያለ አንድ ወጣት አጎንብሶ የሆነ ነገር በማንሳት ወደ ውቆያኖስ ውስጥ ሲጥል ከሩቅ ያየዋል፡፡ እየተጠጋ ሲሄድ እያነሳ ወደውሃ ውስጥ የሚመልሰው ኮከበ...
-
የተጠሩ ብዙዎች፥ የተመረጡ ግን ጥቂቶች ናቸውና። የማቴዎስ ወንጌል 22፡14 እግዚአብሄር ቅን ፈራጅ ነው፡፡ እግዚአብሄር እውነተኛ ዳኛ ነው፡፡ እግዚአብሄር ለሁሉም ሰው እኩል እድልን ይሰጣል፡፡ እግዚአብ...
-
እኔ ግን እላችኋለሁ፥ ክፉውን አትቃወሙ፤ ዳሩ ግን ቀኝ ጉንጭህን በጥፊ ለሚመታህ ሁሉ ሁለተኛውን ደግሞ አዙርለት፤ ማቴዎስ 5፡39 በህይወቱ የሚያየውን ክፉ ሁሉ በክፉ ለመመለስ የሚያስብ ሰው ...
-
በሃጢያት ጨለማ በጠፋሁ ጊዜ ፈልጎ ያገኘኝን የክርስቶስን እውቀት ብርሃን በልቤ ያበራን እግዚአብሄርን ማመስገን አለብኝ፡፡ ሳላውቀው ሳልረዳው ስለሃጢያቴ የሞተልኝን እግዚአብሄርን የማመስገን ግዴታ አለብኝ፡፡ ከልጅነቴ...
-
የእናንተ ሥርና መሠረት በፍቅር ይጸና ዘንድ፥ ከቅዱሳን ሁሉ ጋር ስፋቱና ርዝመቱ ከፍታውም ጥልቅነቱም ምን ያህል መሆኑን ለማስተዋል፥ ከመታወቅም የሚያልፈውን የክርስቶስን ፍቅር ለማወቅ ...
-
ስለኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን እምነት ሲነሳ ስለቅዱሳንና መላእክት ስግደት ፣ ስለማርያም አማላጅነት ስለመሳሰሉት ይነሳል፡፡ ይህ ሁሉ ግን ዋና ነገር አይደለም፡፡ ምንም እንኳን የምናምናቸው መፅሃፍ ቅዱሳዊ ያልሆኑ ነገሮች...
-
በሰው ህይወት ውስጥ ግንኙነት እጅግ በጣም አስፈላጊ እንደመሆኑ መጠን ግንኙነት በትክክል እንዲሰራ የሚያስችለው ነዳጁ ፍቅር ነው፡፡ ፍቅር በጣም አስፈላጊ ነገር ቢሆንም ስለፍቅር ብዙ የተባለና የተፃፈ ቢሆንም ...
Tuesday, June 29, 2021
Tuesday, June 22, 2021
ለፀፀት እንቢ እንበል!
ፀፀት አንድ ሰው በሠራው ነገር ወይም አንድን ነገር ባለማድረጉ የሚሰማው የሐዘን ወይም የቁጭት ስሜት ነው፡፡
ህይወት በውሳኔ የተሞላ ነው፡፡ በህይወታችን በየደቂቃውና
በየሰከንዱ ቅድሚያ የሚሰጠውን ነገር በመለየት ሂደት ብዙ ውሳኔዎችን እንወስናለናን፡፡ በህይወታችን ትንሽ ከሚባለው ነገር ጀምሮ
ትልቅ እስከሚባለው ውሳኔ ድረስ አማራጮችን አመዛዝነን ውሳኔዎችን እንወስናለን፡፡
በየቀኑና በየደቂቃው አንድን ነገር ለማድረግ ወይም
ላለማድረግ መወሰን ተፈጥሮአዊ ግዴታ ነው፡፡ አንድን ነገር ለማድረግ በወሰንን በዚያው ቅፅበት ሌላውን አማራጭ ላለማድረግ እየወሰንን
ነው፡፡ አንድን ነገር ላለማድረግ በወሰንን ቅፅበት ሌላውን አማራጭ ለማድረግህ እየወሰንን ነው፡፡
ውሳኔ ስንወስን ያለንን እውቀት ፣ ማስተዋል እና
ጥበብ ሁሉ ተጠቅመን እንወስናለን፡፡ አብዛኛውን ጊዜ የምንወስነው ላለንበት ጊዜ እና ላለንበት ሁኔታ የተሻለውንና ትክክል የሆነውን
ውሳኔ ነው፡፡ ለነበርንበት ሁኔታ ከዚያ ከወሰነው ውሳኔ በላይ ልንወስን እንችልም ነበር፡፡
ታዲያ ችግሩ የሚመጣው የህይወት ተግዳሮት ሲደርስብን
አንድ ቀን የወሰንነውን ውሳኔ መጠራጠር ስንጀምር ነው፡፡
ልጆች ሆነን አደጋ ስለ ደረሰበት ልጅ ወላጆቻችን
ሲያወሩ እንሰማ ነበር፡፡ ታዲያ ልጁ አደጋ ሳይደርስበት በፊት የጠየቀው ጥያቄ ፣ የፈለገው ፍላጎት እና የለመንው ልመና ሁሉ ለፀፀት
ምክኒያት ሆኖ ሲቀርብ እንሰማ ነበር፡፡ ልጁ ሱቅ ከመላኩ በፊት እማዬ ርቦኛል ብሎ እናቱ ምሳ አልደረሰም ስትመጣ ትበላለህ ብላው
ከሄደ ምነው በሰጠሁትና በበላ ኖሮ ብላ ትፀፀታለች፡፡
ደግም እንፀፀት ካልን የማይፀፅት ነገር የለም፡፡
ለፀፀት ፊት ከሰጠነው በቁማችን ሊውጠን የሚችል ክፉ ሃይል ያለው ነገር ነው፡፡
የሰውን ህይወት ለመስረቅ ለማረድና ለማጥጭፋት
ፀፀተን የሚጠቀመው ሰይጣን ነው፡፡ ሰይጣን እኛን ለማሰቃየት ብዙ የህይወትን ተግዳሮት ያለፍንባቸውን ውሳኔዎች አይጠቀምባቸውም፡፡
በህይወታችን የወሰናቸውን አያሌ ውሳኔዎች እኛን ፀፀት ውስጥ ለመክተት ብዙ ጊዜ አይመቹትም፡፡
ነገር ግን የሰይጣን ብቸኛ አላማ መስረቅ ማረድና ማጥፋት ስለሆነ እንደ አጋጣሚ
ከውሳኔያችን በኋላ የተፈጠረውን ነገር ግን ከውሳኔያችን ጋር ምንም የማይገናኘውን ሁኔታ እያስታወሰ ሊያሰቃየን ይሞክራል፡፡ የሰይጣን
አላማ እኛን ዝቅ ዝቅ ማድረግህ ነው፡፡ የሰይጣን አላማ እኛን በፀፀት ሽባ እድርጎ ዛሬን እና ነገን ለእግዚአብሄር እንዳንኖር ማድረግ
ነው፡፡
እግዚአብሄር ይመራናል ያስጠንነቅናል እንጂ በፀፀት አያሰቃየንም፡፡
እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የሆነ ኀዘን ጸጸት የሌለበትን፥ ወደ መዳንም የሚያደርሰውን
ንስሐ ያደርጋልና፤ የዓለም ኀዘን ግን ሞትን ያመጣል። 2ኛ ቆሮንቶስ 7፡10
አብዛኛውን ጊዜ የምንንፀፀትበት ነገር እግዚአብሄር የሌለበት ነገር ነው፡፡ የእግዚአብሄር
መንፈስ ወቀሳ የሚያበረታታ ፣ የተሻልን ሰዎች እንድንሆን የሚያደርግ እና የተሻለ አድርጎ የሚያስነሳ እና ተስፋ የሚሰጥ እንጂ ባለፈው
ህይወታችን ውስጥ በፀፀት በመኖር ዛሬን እና ወደፊታችንን እንድናባክነው የሚያደርግ አይደለም፡፡
ለፀፀት እንቢ እንበል!
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች
https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/
ለቪዲዮ መልእክቶች
https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ፀፀት #መካድ #መታለል #ታማኝነት #ክህደት #ንስሃ #ሃዘን #መመለስ #መሰደድ #ሃዋሪያዊ #መውደቅ #አለመመረጥ #ተቀባይነትማጣት #ዋጋአሰጣጥ #አእምሮ #ልብ #ኢየሱስ #ጌታ #መፅሃፍቅዱስ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #አምልኮ #እምነት #መከተል
Wednesday, June 9, 2021
መተቸት በጣም ቀላል ነው ፡፡ ሰዎች ሲተቹ እሰማለሁ እናም ስለ መሪዎቻችን እንደማይጸልዩ አውቃለሁ; ስለ ሌሎች በምንጸልይበት ጊዜ እነሱን ለመንቀፍ በጣም ተስማሚ አይደለንምና ፡፡ እኛ ክርስቲያኖች ግን ፖለቲካን ከክርስቶስ በፊት ማስቀደም የለብንም ፡፡ አንዳንድ ሰዎች ከመጠን በላይ በፖለቲካ አስተሳሰብ ውስጥ በመያዛቸው የተነሳ ጥሩ መንፈሳዊ ሰዎች መሆን አይችሉም ፡፡ ኬኔዝ ኢ ሀጊን የሚማልዱ ክርስትያኖች It's so easy to criticize. I hear people criticize and I know they are not praying for our leaders; for when we pray for others we are not so apt to criticize them. As Christians, however, we are not to put politics before Christ. Some people are so politically minded they are no good spiritually. Kenneth E Hagin The Interceding Christians
መተቸት
በጣም ቀላል ነው ፡፡ ሰዎች ሲተቹ እሰማለሁ እናም ስለ መሪዎቻችን እንደማይጸልዩ አውቃለሁ; ስለ ሌሎች በምንጸልይበት ጊዜ እነሱን ለመንቀፍ በጣም ተስማሚ አይደለንምና ፡፡
እኛ
ክርስቲያኖች ግን ፖለቲካን ከክርስቶስ በፊት ማስቀደም የለብንም ፡፡ አንዳንድ ሰዎች ከመጠን በላይ በፖለቲካ አስተሳሰብ ውስጥ በመያዛቸው የተነሳ ጥሩ መንፈሳዊ ሰዎች መሆን አይችሉም ፡፡ ኬኔዝ ኢ ሀጊን የሚማልዱ ክርስትያኖች
It's
so easy to criticize. I hear people criticize and I know they are not praying
for our leaders; for when we pray for others we are not so apt to criticize
them.