Popular Posts

Saturday, April 4, 2020

ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል?


ማንም፦ እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል? 1 የዮሐንስ መልእክት 4:20
ፍቅር ረቂቅ ሃሳብ ነው፡፡ ሰው እግዚአብሄርን እወደዋለሁ ቢል እግዚአብሄርን አትወድም ብለን መከራከር አንችልም፡፡ ሰው እግዚአብሄርን እወዳለሁ ሲል እውነተኝነቱን በቀጥታ ለማረጋገጥ ቀላል አይደለም፡፡ ምክኒያቱም ፍቅር የልብ ስለሆነና የሰው ልብ ደግሞ ተከፍቶ ስለማይታይና ስለማይታወቅ ነው፡፡
ፍቅር የልብ መሰጠት ስለሆነ ሰው እግዚአብሄርን መውደዱ የሚረጋገጥበት ቀጥተኛ መንገድ የለም፡፡ ሰው እግዚአብሄርን መውደዱንና አለመውደዱን በቀጥታ ሳይሆን በተዘዋዋሪ የሚያመለክቱ ነገሮች ግን አሉ፡፡ እኛም እግዚአብሄርን እንዴት እንድምንወድ የምንፈትንባቸው ሌሎች መንገዶች አሉ፡፡
ሰው እግዚአብሄርን መውደዱ መለኪያው ሰውን መውደዱ ነው፡
ሰውን የመውደድ ጥቂቱን መመዘኛ የማያማላ ሰው እግዚአብሄርን እወዳለሁ ቢል ውሸቱን ነው፡፡ ሰው የሚያየውን ሰው ካልወደደ የማያየውን እግዚአብሄርን እንደማይወድ በቂ ማረጋገጫ ነው፡፡
ለሰው ቅርቡ የሚያየውን ሰውን መውደድ ነው፡፡ ለሰው የሚቀለው ለሚያየው ሰው መልካምን ማድረግ ነው፡፡ ለሰው የሚቀለው የሚያየውን ሰውን በርህራሄ ማየት ነው፡፡ ለሰው የሚቀለው የሚያየውን የሚዳስሰውን ሰውን መቀበል ነው፡፡ ለሰው የሚቀለው የሚያየውን ሰውን መታገስ ነው፡፡ ለሰው የሚቀለው ከሚያየውን ሰው ጋር በትህትና መኖር ነው፡፡
ሰው እግዚአብሄርን እወዳለሁ እግዚአብሄርን አከብራለሁ የሚለው ለእግዚአብሄር ያለን አክብሮት ለሰው እንዳለን አክብሮት በቀጥታ የማይታይ ስለሆነ ይሆናል፡፡ ሰው ለእግዚአብሄር ፍቅር አለኝ የሚለው ስለማይታይ ይሆናል፡፡ ሰው በእግዚአብሄር ፊት ትሁት ነኝ የሚለው በቀጥታ ትህትናው በቀጥታ ስለማይለካ ይሆናል፡፡
ሰው ለሚያየው ሰው መልካምን ካላደረገ ለእግዚአብሄር መልካም ያደርጋል ማለት ዘበት ነው፡፡ ሰው የሚያየውን ሰውን ካልተቀበለ የማያየውን እግዚአብሄርን ይቀበላል ማለት ውሸት ነው፡፡ ሰው የሚያየውን ሰውን በርህራሄ ካላየ የማያየውን እግዚአብሄርን ይወዳል ማለት ከንቱ ነው፡፡ ሰው የሚያየውን ሰው ካልታገሰ እግዚአብሄርን እታገሳለሁ ማለቱ ከእውነት የራቀ ነው፡፡ ሰው ከሚያየው ከሰው ጋር በትህትና መኖር ካልቻለ እኔ በእግዚአብሄር ፊት ትሁት ነኝ ቢል ተታልሎዋል፡፡
ማንም፦ እግዚአብሔርን እወዳለሁ እያለ ወንድሙን ቢጠላ ሐሰተኛ ነው፤ ያየውን ወንድሙን የማይወድ ያላየውን እግዚአብሔርን ሊወደው እንዴት ይችላል? 1ኛ የዮሐንስ መልእክት 4:20
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa37/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#ኢየሱስ #ጌታ #ሰላም #እምነት #ሃሳብ #ጥበብ #ማስተዋል #ፍቅር #ትህትና #ርህራሄ #መልካም #ጠብ #መልካም #ፍርድ #እውቅና #ፍፁም #ችግር #መፍትሄ #አላማ #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ  #እምነት #ቃል  #ማደስ #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ

No comments:

Post a Comment