I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ጸሎት ከእግዚአብሄር ጋር መነጋገር ነው። ጸሎት ሊደረግ የሚችለው ከእግዚአብሄር ጋር በመግባባት ብቻ ነው። ጸሎት የሚሰምረው እንደ እግዚአብሄር አሳብ ስንጸልይ ብቻ ነው። በአጠቃላይ ለእግዚአብሄር ያለን አመለካከት ...
-
ፈተና ለእኛ መልስ የሌለው ጥያቄ ነው፡፡ በህይወት መልስ የሌለው ጥያቄ የለም፡፡ በህይወት መውጫ የሌለው ፈተና የለም፡፡ ፈተና የለም ማለት ስህተት እንደሆነ ሁሉ ፈተናው መልስ የለውም ማለት እንዲሁ ስህተት ነው፡፡ ፈተ...
-
There are different seasons in our lives. There is a season to live with others there is a season to go our way. Seasons definitely cha...
-
በተለያየ ጊዜ በህይወታችን የተለያዩ ተግዳሮቶች ይመጣሉ፡፡ ታዲያ ይህን አልፈው ይሆን ብለን የምናስብበት ውጥረት በህይወታችን ይመጣል፡፡ እንደዚህ አይነት ውጥረት በህይወታችን ሲገጥመን "በምድር ላይ ያለሁት ለ...
-
ክርስቶስ ስለሃጢያታችን ከቃሉ በመስቀል ላይ እንደሞተ ከቃሉ ስናይ ደህንነታችንን እንቀበላለን፡፡ እንዲሁም ኢየሱስ ስለሃጢያታችን መገረፉን ከልባችን ስንረዳ በሽታ በእኛ ላይ አቅም አይኖረውም፡፡ የሰው ፈውስ በመስቀል ...
-
… From Oppressive Obligations to Incredible Opportunities The phone isn’t just ringing, it seems to be screaming. You’ve got yet another...
-
አንድነት ተመሳሳይነት አይደለም፡፡ አንድነት በአንድ ጣራ ስር መሰብሰብ አይደለም፡፡ አንድነት ተመሳሳይ ነገር ማሰብ እና ማድረግ አይደለም፡፡ አንድነት ተመሳሳይ ስጦታ መኖር አይደለም፡፡ አንድነትን በተመሳሳይነት መ...
-
አስቀድማችሁ ከፈሪሳውያን እርሾ ተጠበቁ! ክፍል 7 ባስተላለፋችሁትም ወግ የእግዚአብሔርን ቃል ትሽራላችሁ፤ እንደዚሁም ይህን የሚመስል ብዙ ነገር ታደርጋላችሁ። የማርቆስ ወንጌል 7፡13 ፈሪሳዊያን እንጅ ታጥቦ ስለ መብላይ...
-
ለሃጢያታችን ለመስቀልና ለመሞት ኢየሱስ ክርስቶስ ወደዚህ መድር የመጣው በማርያም አማካኝነት ነው፡፡ ማርያም የኢየሱስ እናት ለመሆን በእግዚአብሄር የተመረጠች ሴት ነች፡፡ መልእክቱን ለእለት ተእለት ህይወታችን ትምህር...
Thursday, April 23, 2020
እንዲህም ይሆናል፤ የአምላክህን የእግዚአብሔርን ቃል ብትሰማ፥ ዛሬም ያዘዝሁህን ትእዛዙን ሁሉ ብታደርግ ብትጠብቅም፥ አምላክህ እግዚአብሔር ከምድር አሕዛብ ሁሉ ላይ ከፍ ከፍ ያደርግሃል። የአምላክህንም የእግዚአብሔርን ቃል ብትሰማ እነዚህ በረከቶች ሁሉ ይመጡልሃል ያገኙህማል። አንተ በከተማ ቡሩክ ትሆናለህ፥ በእርሻም ቡሩክ ትሆናለህ። የሆድህ ፍሬ፥ የምድርህም ፍሬ፥ የከብትህም ፍሬ፥ የላምህም ርቢ፥ የበግህም ርቢ ቡሩክ ይሆናል። እንቅብህና ቡሃቃህ ቡሩክ ይሆናል። አንተም በመግባትህ ቡሩክ ትሆናለህ፥ በመውጣትህም ቡሩክ ትሆናለህ። እግዚአብሔርም በላይህ የሚቆሙትን ጠላቶችህን በፊትህ የተመቱ ያደርጋቸዋል፤ በአንድ መንገድ ይመጡብሃል፥ በሰባትም መንገድ ከፊትህ ይሸሻሉ። እግዚአብሔር በረከቱ በአንተ ላይ በጐተራህ በእጅህም ሥራ ሁሉ እንዲወርድ ያዝዛል፤ አምላክህ እግዚአብሔር በሚሰጥህም ምድር ይባርክሃል። የአምላክህን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ብትጠብቅ፥ በመንገዱም ብትሄድ፥ እግዚአብሔር እንደ ማለልህ ለእርሱ የተቀደሰ ሕዝብ አድርጎ ያቆምሃል። የምድር አሕዛብም ሁሉ የእግዚአብሔር ስም በአንተ ላይ እንደ ተጠራ አይተው ይፈሩሃል። እግዚአብሔርም እርስዋን ይሰጥህ ዘንድ ለአባቶችህ በማለላቸው በምድርህ ላይ፥ በሆድህ ፍሬ፥ በከብትህ ፍሬ፥ በእርሻህም ፍሬ፥ እግዚአብሔር በጎነቱን በላይህ ያበዛል። እግዚአብሔርም ለምድርህ በወራቱ ዝናብ ይሰጥ ዘንድ፥ የእጅህንም ሥራ ሁሉ ይባርክ ዘንድ መልካሙን መዝገብ ሰማዩን ይከፍትልሃል፤ ለብዙ አሕዝብም ታበድራለህ፥ አንተ ግን ከማንም አትበደርም። ዛሬም ያዘዝሁህን የአምላክህን የእግዚአብሔርን ትእዛዝ ሰምተህ ብትጠብቃት ብታደርጋትም፥ ዛሬም ካዘዝሁህ ከእነዚህ ቃሎች ወደ ቀኝ ወደ ግራም ፈቀቅ ባትል፥ ታመልካቸውም ዘንድ ሌሎችን አማልክት ባትከተል፥ እግዚአብሔር ራስ ያደርግሃል እንጂ ጅራት አያደርግህም፤ ሁልጊዜም በላይ እንጂ በታች አትሆንም። ኦሪት ዘዳግም 28፡1-14
Subscribe to:
Post Comments (Atom)

No comments:
Post a Comment