I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
በአለማችን ላይ እውነተኛ ደቀመዛሙርቶች አሉ፡፡ የስም ብቻ ደቀመዛሙርቶች ደግሞ አሉ፡፡ እውነተኛ ደቀመዝሙር የሚያደርገን ምን እንደሆነ ማወቅ በጣም ወሳኝ ነገር ነው፡፡ የእውነተኛ ደቀመዝሙርነት መንገድ ላይ መሆናችንን ...
-
Live soberly and be vigilant, for the devil, who is not your partner, prowls around like a roaring lion looking for someone to devour. Re...
-
እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር ፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ...
-
ተጠማው እልውናህን መገኘትህን ጌታ ድምጽህን መዓዛ ግርማህን አልፈልግም ኖረ ኖረ ኖረ ሞተ አልፈልግም መሆን በምድር የታመነ መንፈስክን ይዞ ይዞ ሚገሰግስ ለተጠማው ደርሶ የልብህን የሚያደር...
-
https://youtu.be/VhF0pSsp14I በቃልኪዳን መነጽር ህይወታችን ማየት አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa ሬማ እምነት አገልግሎት በርሚንግሃም ቤተክርስትያን
-
ፍቅር እጅግ አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ ሰው ለፍቅር ተፈጥሯል፡፡ የሰውን ህይወት የሚያጣፈጠው ፍቅር ነው፡፡ ለሰው ውበትን የሚሰጠው ፍቅር ነው፡፡ ለሰው ጣእምን የሚሰጠው ፍቅር ነው፡፡ ለሰው ሞገስን የሚሰጠው ፍቅር ...
-
ሰው በእግዚአብሄር አምሳል ተፈጥሮአል፡፡ ሰው ለእግዚአብሄር ክብር ተፈጥሯል፡፡ ሰው የተፈጠረበትን አላማ አግኝቶ ካልፈፀመው ህይወቱን ያባክናል፡፡ ሰው እግዚአብሄር ለእርሱ ያለውን አላማ አግኝቶ ከፈፀመው ግን በህይወት ...
-
ነቢይ የእግዚአብሄር አፍ ነው፡፡ ነቢይ ከለአግዚአብሄር ሰምቶ የሚናገር ነው፡፡ ነቢይ የእግዚእብህር በልቡና ያለውን ተረድቶ ለህዝቡ የሚገልፅ ነው፡፡ በድሮ ዘመን ብቻ ሳይሆን እግዚአብሄር ነቢይን በዚህ በእኛ ዘመን ...
-
ቀራጮችም ደግሞ ሊጠመቁ መጥተው፦ መምህር ሆይ፥ ምን እናድርግ ? አሉት። ከታዘዘላችሁ አብልጣችሁ አትውሰዱ አላቸው። ጭፍሮችም ደግሞ፦ እኛ ደግሞ ምን እናድርግ ? ብለው ይጠይቁት ነበር። ...
-
Bait your hook an' keep a- tryin '-- Keep a-goin '! When the weather kills your crop, Keep a-goin '! Though 'tis...
Sunday, May 31, 2020
የነፍስ ብቻ ሳይሆን የስጋ ፈውስ ያስፈልገናል
Friday, May 29, 2020
Thursday, May 28, 2020
Tuesday, May 26, 2020
ትንቢተ ኢሳይያስ ምዕራፍ 53
1፤ የሰማነውን ነገር ማን አምኖአል? የእግዚአብሔርስ ክንድ ለማን ተገልጦአል?
2፤ በፊቱ እንደ ቡቃያ ከደረቅም መሬት እንደ ሥር አድጎአል። መልክና ውበት የለውም፥ ባየነውም ጊዜ እንወድደው ዘንድ ደም ግባት የለውም።
3፤ የተናቀ ከሰውም የተጠላ፥ የሕማም ሰው ደዌንም የሚያውቅ ነው፤ ሰውም ፊቱን እንደሚሰውርበት የተናቀ ነው፥ እኛም አላከበርነውም።
4፤ በእውነት ደዌያችንን ተቀበለ ሕመማችንንም ተሸክሞአል፤ እኛ ግን እንደ ተመታ በእግዚአብሔርም እንደ ተቀሠፈ እንደ ተቸገረም ቈጠርነው።
5፤ እርሱ ግን ስለ መተላለፋችን ቈሰለ፥ ስለ በደላችንም ደቀቀ፤ የደኅንነታችንም ተግሣጽ በእርሱ ላይ ነበረ፥ በእርሱም ቍስል እኛ ተፈወስን።
6፤ እኛ ሁላችን እንደ በጎች ተቅበዝብዘን ጠፋን፤ ከእኛ እያንዳንዱ ወደ ገዛ መንገዱ አዘነበለ፤ እግዚአብሔርም የሁላችንን በደል በእርሱ ላይ አኖረ።
7፤ ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ ለመታረድ እንደሚነዳ ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።
8፤ በማስጨነቅና በፍርድ ተወሰደ፤ ስለ ሕዝቤ ኃጢአት ተመትቶ ከሕያዋን ምድር እንደ ተወገደ ከትውልዱ ማን አስተዋለ?
9፤ ከክፉዎችም ጋር መቃብሩን አደረጉ፥ ከባለጠጎችም ጋር በሞቱ ሆኖም ግፍን አላደረገም ነበር፥ በአፉም ተንኮል አልተገንበትም ነበር።
10፤ እግዚአብሔርም በደዌ ያደቅቀው ዘንድ ፈከደ፤ ነፍሱን ስለ ኃጢአት መሥዋዕት ካደረገ በኋላ ዘሩን ያያል፥ ዕድሜውም ይረዝማል፥ የእግዚአብሔርም ፈቃድ በእጁ ይከናወናል።
11፤ ከነፍሱ ድካም ብርሃን ያያል ደስም ይለዋል፤ ጻድቅ ባሪያዬም በእውቀቱ ብዙ ሰዎችን ያጸድቃል፥ ኃጢአታቸውን ይሰከማል።
12፤ ስለዚህም እርሱ ብዙዎችን ይወርሳል፥ ከኃያላንም ጋር ምርኮን ይከፋፈላል፤ ነፍሱን ለሞት አሳልፎ ሰጥቶአልና፥ ከዓመፀኞችም ጋር ተቈጥሮአልና፤ እርሱ ግን የብዙ ሰዎችን ኃጢአት ተሸከመ፥ ስለ ዓመፀኞችም ማለደ።
Monday, May 25, 2020
የደስታ ያለህ
ክርስቲያናዊ ደስታን አፈላለግ በሚቀጥሉት አምስት እምነቶች ላይ የተገነባ የህይወት መረዳት ነው፡፡
l. ደስተኛ ለመሆን መጓጓት አለም አቀፋዊ ሁለንተናዊ የሰዎች ምኞት ነው፡፡ ደስተኛ ለመሆን የመመኘት ልምምድ መልካም እና ምንም ክፋት የሌለበት ነገር ነው፡፡
2. መጥፎ ስሜት ይመስል ደስተኛ የመሆን ምኞታችንን ለመካድ ወይም ለመቃወም በፍጹም መሞከር የለብንም፡፡
ይልቁን ጥልቅ እና በጣም ዘላቂ እርካታን ለማግኘት ይህንን ምኞት ማጠንከር እና ማዳበር አለብን፡፡
3. እጅግ ጥልቅ እና ዘላቂ ደስታ የሚገኘው በእግዚአብሄር ውስጥ ብቻ ነው፡፡
4. በእግዚአብሔር የምናገኘው ደስታ ከሌሎች ጋር በፍቅር ሲጋራ ወደ ደስታ ፍጻሜ ይደርሳል፡፡
5. የራሳችንን ደስታ ለማሳደድን እስከሞከርን
ጊዜ ድረስ ግን እግዚአብሄርን ማክበርና ሰውን መውደድ ያቅተናል፡፡
በሌላ አነጋገር የሰው ልጅ ዋናው ፍፃሜ በእግዚአብሄር
ለዘላለም ደስ በመሰኘት እርሱን ማክበር ነው፡፡
From the Book Desiring God by
John Piper Page 16.
Tuesday, May 19, 2020
Wednesday, May 13, 2020
ስጡ
ስጡ ይሰጣችሁማል፤ በምትሰፍሩበት መስፈሪያ ተመልሶ ይሰፈርላችኋልና፥ የተጨቈነና የተነቀነቀ የተትረፈረፈም መልካም መስፈሪያ በእቅፋችሁ ይሰጣችኋል። የሉቃስ ወንጌል 6፡38
ይህ የኢየሱስ ንግግር ስለመስጠት እንጂ ስለ መቀበል
የተደረገ ንግግር አይደለም፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች ይህን ክፍል ስለመቀበል ይሰብኩታል፡፡ የዚህ የመስጠት ትምህርት አላማ ግን መስጠት
እንጂ በፍፁም መቀበል አይደለም፡፡
ሰው ሲሰጥ ወደ አእምሮው የሚመጣ ጥያቄ አለ፡፡
ስሰጥ እኔስ ቢጎድልብኝ የሚል ጥያቄ በሁላችንም አእምሮ ውስጥ ይመላለሳል፡፡
ሰጥቼ እኔስ ቢጎድልብኝ የሚለው ጥያቄ የሚፈጠርብን
ምክኒያት ገንዘብ ጊዜያዊም ቢሆን የመተማመን ስሜትን ስለሚሰጠን ነው፡፡
በአጠቃላይ አለምን የሚያንቀሳቅሰው የእግዚአብሄር
ፍቅር ወይም የገንዘብ ማጣት ፍርሃት ነው፡፡ ሰው እንዳያጣ ብዙ ነገሮችን ያደርጋል፡፡
እንግዲህ፦ ምን እንበላለን?
ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። የማቴዎስ ወንጌል 6፡31-32
ሰው ገንዘቡን ለመስጠት የሚገዳደረው ምክኒያት
ገንዘብ የመተማመን ስሜትን በሰው ውስጥ ስለሚፈጥር ነው፡፡
ታዲያ ገንዘባችንን ስንሰጥ የምንሰጠው መተማመኛችንን
ነው፡፡ ገንዘባችንን ለመስጠት ከገንዘብ በላይ የምንተማመንበት እግዚአብሄርን ማመን ይጠይቃል፡፡ ገንዘብ ለመስጠት ከሚታየው ያለፈ
የእግዚአብሄርን መንግስት አሰራር በእምነት አይን ማየት ይጠይቃል፡፡ ገንዘብን ለመስጠት የእግዚአብሄርን ቃል ማመን ይጠይቃል፡፡
ለዘሪ ዘርን ለመብላትም እንጀራን በብዙ የሚሰጥ እርሱም የምትዘሩትን ዘር ይሰጣችኋል ያበረክትላችሁማል፥ የጽድቃችሁንም ፍሬ ያሳድጋል፤ 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9፡10
ስጡ ብሎ ኢየሱስ ይሰጣችኋል ያለበት ምክኒያት
በሰው ውስጥ የሚነሳውን ሰጥቼ ቢጎድልብኝስ? የሚለውን ጥያቄ ለመመለስ ነው፡፡ ስጡ ብሎ መልሱ ባጣስ ለሚለው ጥያቄ መልሱ ስለሰጣችሁ
አይጎድልባችሁም የሚለው ነው፡፡ ስለሰጣችሁ አታጡም ስለሰጣችሁ አትከስሩም፡፡
ይህንም እላለሁ፦ በጥቂት የሚዘራ በጥቂት ደግሞ ያጭዳል፥ በበረከትም የሚዘራ በበረከት ደግሞ ያጭዳል። 2ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 9፡6
ስትሰጡ ይሰጣችሁዋል፡፡ ስትሰጡ ይጨመርላችሁዋል፡፡
ስትሰጡ ይበልጥ ይሰጣችሁዋል፡፡
ስጡ ይሰጣችሁማል፤ በምትሰፍሩበት መስፈሪያ ተመልሶ
ይሰፈርላችኋልና፥ የተጨቈነና የተነቀነቀ የተትረፈረፈም መልካም መስፈሪያ በእቅፋችሁ ይሰጣችኋል። የሉቃስ ወንጌል 6፡38
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.dinsa.37/notes
ለቪዲዮ መልእክቶች
https://www.youtube.com/user/awordm/videos
#እረፍት #ቅድሚያ #እምነት
#መደገፍ #ሰንበት
#መዝራት #ማጨድ #ፅድቁን #ኢየሱስ #ክርስቶስ #ጌታ
#ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #እምነት #መፅሃፍቅዱስ
#መንፈስቅዱስ #ምህረት
#ፌስቡክ #አቢይዋቁማ
#አቢይዋቁማዲንሳ







