I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
እንግዲህ እግዚአብሔርን በመምሰልና በጭምትነት ሁሉ ጸጥና ዝግ ብለን እንድንኖር ፥ ልመናና ጸሎት ምልጃም ምስጋናም ስለ ሰዎች ሁሉ ስለ ነገሥታትና ስለ መኳንንትም ሁሉ እንዲደረጉ ከሁሉ...
-
ተጠማው እልውናህን መገኘትህን ጌታ ድምጽህን መዓዛ ግርማህን አልፈልግም ኖረ ኖረ ኖረ ሞተ አልፈልግም መሆን በምድር የታመነ መንፈስክን ይዞ ይዞ ሚገሰግስ ለተጠማው ደርሶ የልብህን የሚያደር...
-
https://youtu.be/VhF0pSsp14I በቃልኪዳን መነጽር ህይወታችን ማየት አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa ሬማ እምነት አገልግሎት በርሚንግሃም ቤተክርስትያን
-
Live soberly and be vigilant, for the devil, who is not your partner, prowls around like a roaring lion looking for someone to devour. Re...
-
ፍቅር እጅግ አስፈላጊ ነገር ነው፡፡ ሰው ለፍቅር ተፈጥሯል፡፡ የሰውን ህይወት የሚያጣፈጠው ፍቅር ነው፡፡ ለሰው ውበትን የሚሰጠው ፍቅር ነው፡፡ ለሰው ጣእምን የሚሰጠው ፍቅር ነው፡፡ ለሰው ሞገስን የሚሰጠው ፍቅር ...
-
በአለማችን ላይ እውነተኛ ደቀመዛሙርቶች አሉ፡፡ የስም ብቻ ደቀመዛሙርቶች ደግሞ አሉ፡፡ እውነተኛ ደቀመዝሙር የሚያደርገን ምን እንደሆነ ማወቅ በጣም ወሳኝ ነገር ነው፡፡ የእውነተኛ ደቀመዝሙርነት መንገድ ላይ መሆናችንን ...
-
ሰው በእግዚአብሄር አምሳል ተፈጥሮአል፡፡ ሰው ለእግዚአብሄር ክብር ተፈጥሯል፡፡ ሰው የተፈጠረበትን አላማ አግኝቶ ካልፈፀመው ህይወቱን ያባክናል፡፡ ሰው እግዚአብሄር ለእርሱ ያለውን አላማ አግኝቶ ከፈፀመው ግን በህይወት ...
-
ቀራጮችም ደግሞ ሊጠመቁ መጥተው፦ መምህር ሆይ፥ ምን እናድርግ ? አሉት። ከታዘዘላችሁ አብልጣችሁ አትውሰዱ አላቸው። ጭፍሮችም ደግሞ፦ እኛ ደግሞ ምን እናድርግ ? ብለው ይጠይቁት ነበር። ...
-
Bait your hook an' keep a- tryin '-- Keep a-goin '! When the weather kills your crop, Keep a-goin '! Though 'tis...
-
ነቢይ የእግዚአብሄር አፍ ነው፡፡ ነቢይ ከለአግዚአብሄር ሰምቶ የሚናገር ነው፡፡ ነቢይ የእግዚእብህር በልቡና ያለውን ተረድቶ ለህዝቡ የሚገልፅ ነው፡፡ በድሮ ዘመን ብቻ ሳይሆን እግዚአብሄር ነቢይን በዚህ በእኛ ዘመን ...
Monday, May 13, 2019
የደስተኝነት ምርጫ
በህይወት ደስተኛ መሆን የእድል ጉዳይ ሳይሆን የምርጫ ጉዳይ ነው:: ሰው ሁሉ ደስተኛ መሆን ይፈልጋል:: ነገር ግን ሰው ሁሉ ደስተኛ የሚያደርገውንነገር አይመርጥም:: እንዳንድ ሰው ደስተኛ ለመሆን ቢፈልግም ደስተኛ የሚያደርጉትን ሳይሆን ደስተኛ የማያደጉትን ነገሮች ስለሚመርጥ ደስተኛ ሳይሆን ጊዜውን ያባክናል::
ክፉ ሀዘን ጉልበትን ያደክማል:: ክፉ ሀዘን የኑሮ መነሳሳትን ይገድለዋል::
እርሱም፡— ሂዱ፥ የሰባውንም ብሉ፥ ጣፋጩንም ጠጡ፥ ለእነዚያም ላልተዘጋጀላቸው እድል ፈንታቸውን ስደዱ፤ ዛሬ ለጌታችን የተቀደሰ ቀን ነው፤ የእግዚአብሔርም ደስታ ኃይላችሁ ነውና አትዘኑ፡ አላቸው። መጽሐፈ ነህምያ 8:10
ደስተኝነት ለመኖር ለመስራትና ወደህይወት ግባችን ለመድረስ ጉልበት ይሰጠናል::
በህይወት ደስተኛ የማያደርገንን ነገሮች እስካልመረጥን ድረስ ደስተኛ መሆናችን አይቀርም::
ደስተኛ የማያደርጉ ሀሳቦች
1. ራስን ከሌላ ሰው ጋር ማፎካከር
ደስተኛ ላለመሆን አቋራጩ መንገድ በህይወት የተለያየ የህይወት አላማና ስጦታ ያላቸውን ሰዎች ለማወዳደርና ለማበላለጥ መሞከር ነው::
ራሳቸውን ከሚያመሰግኑ ከአንዳንዶች ጋር ራሳችንን ልንቆጥር ወይም ራሳችንን ልናስተያይ አንደፍርምና፤ ነገር ግን እነርሱ ራሳቸውን ከራሳቸው ጋር ሲያመዛዝኑ፥ ራሳቸውንም ከራሳቸው ጋር ሲያስተያዩ፥ አያስተውሉም። 2ኛ ቆሮንቶስ 10:12
2. ያለፈን ህይወት በፀፀት ለማስተካከል መሞከር
ያለፈ ህይወት አልፎዋል:: ስላለፈ ህይወት መፀፀት ዛሬን መግደል ነው:: ስላለፈ ህይወት መፀፀት ከዛሬ ትላንት ይሻል ነበር ብሎ ዛሬን ማናናቅ ነው::
3. የሌለን ነገር ላይ ማተኮር
የሌለን ነገር ላይ ማተኮር ያለንን ነገር በአግባቡ እንዳንጠቀምበት ያደርገናል:: የሌለን ነገር ላይ ማተኮር ያለንን እንዳናከብረውና እንዳንንቀው ያደርገናል:: የሌለን ነገር እንደማያስፈልገን ምንም ማረጋገጫ የለንም::
4. ያልደረስንበት ደረጃ ላይ ማተኮር
ሁላችንም ህልሞች አሉን:: ነገር ግን አሁን አንዳንዱ ህልማችን እውን ሆኖ እየኖርነው አይደለም ማለት አይደለም:: ከዚህ በፊት ምንም ሆኖልን እንደማያውቅ ምንም አከናውነን እንደማናውቅ የነገ ግባችን ላይ ከመጠን በላይ ማተኮር ደስተኛ ላለመሆን መምረጥ ነው::
5. ከጌታ ውጭ ማተኮር
ሰው የተፈጠረው በእግዚአብሄርና ከእግዚአብሄር ጋር እንዲኖር ነው:: ሰው ግን እግዚአብሄርን ካላሰበ ደስተኛ መሆን ያቅተዋል:: ብዙ ደስ የማያሰኙ ነገሮች በዙሪያችን እያሉ በጌታ ደስ መሰኘት ይቻላል::
ሁልጊዜ በጌታ ደስ ይበላችሁ፤ ደግሜ እላለሁ፥ ደስ ይበላችሁ። ወደ ፊልጵስዩስ 4:4
Subscribe to:
Comments (Atom)