I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ለተሳካ ህይወትና ለአገልግሎት ራእይ ወሳኝ ነገር ነው፡፡ ራእይ ከየት እንደመጣን ወዴት እንደምንሄድ ይጠቁመናል፡፡ አንዳንድ ሰዎች ራእይ ሊጨበጥ የማይችል ሃይማኖታዊ ሃሳብ ብቻ ይመስላቸዋል፡፡ ስለዚህ አንዳንድ ሰዎች...
-
ሰዎችን ሁሉ የሚያድን የእግዚአብሔር ጸጋ ተገልጦአልና፤ ይህም ጸጋ፥ ኃጢአተኝነትንና ዓለማዊን ምኞት ክደን፥ የተባረከውን ተስፋችንን እርሱም የታላቁን የአምላካችንንና የመድኃኒታችንን የኢየሱ...
-
የምድር መሠረቶች የእግዚአብሔር ናቸውና! ABIY WAKUMA DINSA BLOG · SATURDAY, 20 AUGUST 2016 ሰው በምድር ላይ እንዲበረክት አለመታበይ አለበት፡፡ ሰው በምድር ላይ ተቋቁሞ...
-
-
It isn’t only what we do in life that matters it is also why we do the things we do. Even our good activities should be checked as in w...
-
በእኔ ላይ ግን አንድ ነገር እንኳ አይሠለጥንብኝም። መብል ለሆድ ነው፥ ሆድም ለመብል ነው፤ እግዚአብሔር ግን ይህንም ያንም ያጠፋቸዋል። 1 ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 6 ፡ 12-13 ...
-
እኛ በጌታ በኢየሱስ አዳኝነት አምነን የዳንን እና የእግዚአብሄር ልጆች የሆንን ሁላችን የአባታችንን እግዚአብሄርን ፍቅር ተካፍለናል፡፡ የእግዚአብሄር ፍቅር በልባችን ፈሷል፡፡ በተሰጠን...
-
Miracle Everyday God created us for a purpose. He is busy working in our lives. We are created for the supernatural. We see God working in ...
Tuesday, January 31, 2023
Wednesday, January 25, 2023
Thursday, January 19, 2023
Wednesday, January 18, 2023
Tuesday, January 17, 2023
አሕዛብ ለምን ያጕረመርማሉ? ወገኖችስ ለምን ከንቱን ይናገራሉ? የምድር ነገሥታት ተነሡ፥ አለቆችም በእግዚአብሔርና በመሢሑ ላይ እንዲህ ሲሉ ተማከሩ። ማሰርያቸውን እንበጥስ፥ ገመዳቸውንም ከእኛ እንጣል። በሰማይ የሚኖር እርሱ ይሥቃል፥ ጌታም ይሣለቅባቸዋል። በዚያን ጊዜ በቍጣው ይናገራቸዋል፥ በመዓቱም ያውካቸዋል። መዝሙር 2:1-5
አሕዛብ ለምን ያጕረመርማሉ? ወገኖችስ ለምን ከንቱን ይናገራሉ? የምድር ነገሥታት ተነሡ፥አለቆችም በእግዚአብሔርና በመሢሑ ላይ እንዲህ ሲሉ ተማከሩ። ማሰርያቸውን እንበጥስ፥ገመዳቸውንም ከእኛ እንጣል። በሰማይ የሚኖር እርሱ ይሥቃል፥ ጌታም ይሣለቅባቸዋል። በዚያን ጊዜበቍጣው ይናገራቸዋል፥ በመዓቱም ያውካቸዋል። መዝሙር 2:1-5
Sunday, January 15, 2023
Saturday, January 14, 2023
የሁለቱ ቅርጫቶች ወግ
አንድ ልቤን የነካኝን ታሪክ ልንገራችሁ፡፡
እግዚአብሄር ለአንድ አገልጋይ ስለአንዲት የምትፀልይ ሴት ራእይ አሳየው፡፡ በራእዩ ውስጥ ሁለት ቅርጫቶችን ያያል፡፡ አንዱ ቅርጫት ሙሉ ነው አንዱ ቅርጫት ግን ውስጡ ያለበት ነገር እጅግ በጣም ትንሽ ነው፡፡ እግዚአብሄርን ይህ ምንድነው ? ብሎ ስለትርጉሙ ሲጠይቅ ስለሁለቱ ቅርጫቶች እንዲህ ሲል ተናገረው፡፡ እነዚህ ቅርጫቶች የዚህች ሴት የፀሎት እና የምስጋና ህይወትዋ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ይህች ሴት መፀለይ ታውቃለች፡፡ ካለማቋረጥ አብዝታ ትፀልያለች ትጮኻለች፡፡ ይህ የምትመለከተው ሙሉው ጭርጫት የፀሎት ህይወቷ ነው፡፡ ይህ የምትመለከተው እጅግ በጣም ትንሽ ነገር ያለበት ቅርጫት ደግሞ የምስጋና ህይወቷ ነው፡፡ ይህች ሴት መፀለይ ታውቃለች እንጂ ማመስገን አታውቅም፡፡ ስለዚህ ፀሎትዋ እንደሚገባው ውጤታማ አይደለም፡፡
ይህች ሴት ማመስገን ስትጀምር እና የምስጋና ቅርጫትዋ እየሞላ ሲደሄድ የፀለየችው ፀሎትዋ እየተመለሰ ይሄዳል ብሎ እግዚአብሄር አስረዳው፡፡
ይግህ ታሪክ ስለ እያንዳንዳችን የፀሎት ህይወት ወሳኝ ነገርን ያስተምረናል፡፡
ሰው መፀለዩን እንጂ እንዴት በምስጋና ልብ መፀለይ እንዳለበት ካላወቀ በፀሎት ህይወቱ ውጤታማ ሊሆን አይችልም፡፡ ከፀለየ በኋላ እንዴት በማመስገን መቀጠል እንዳለበት የማይረዳ ሰው ፀሎቱ ፍሬያማ መሆን አይችልም፡፡
ከእግዚአብሄር ጋር ያለን ማንኛውም ግንኙነት በምስጋና ልብ መሆን አለበት፡፡ በአጠቃላይ ከእግዚአብሄር ጋር ያለን ግንኙነት በትህትና ለእግዚአብሄር አምላክነት እና መልካምነት እውቅና በመስጠት ካልሆነ ውጤታማ አይሆንም፡፡
በፀሎትም ወደ እግዚአብሄር መቅረብ የህይወታችን እረኛ እንደሆነ ፣ የሚያሳጣን እንደሌለ ፣ በእርሱ አቅርቦት በየእለቱ እንደምንኖር እውቅና መስጠት ይጠይቃል፡፡ ወደ እግዚአብሄር ስንቀርብ በማጉረምረም መሆን የለበትም፡፡ ወይም ደግሞ እግዚአብሄር በትክከል እንዳልያዘን ፣ ምንምም ነገር አድርጎን እንደማያውቅ መቅረብ የለብንም፡፡ ወደ እግዚአብሄር ስንቀርብ ለመጀመሪያ ጊዜ አንድ ነገር ሊያደርግልን እንደሆነ በማንጎራጎር ከሆነ ለአምላክነቱ የሚገባውን እውቅና ስላልሰጠ በፀሎታችን እግዚአብሄር ደስ አይሰኝም፡፡
በደስታም ለእግዚአብሔር ተገዙ፥ በሐሤትም ወደ ፊቱ ግቡ። እግዚአብሔር እርሱ አምላክ እንደ ሆነ እወቁ፤ እርሱ ሠራን እኛም አይደለንም፤ እኛስ ሕዝቡ የማሰማርያውም በጎች ነን። ወደ ደጆቹ በመገዛት፥ ወደ አደባባዮቹም በምስጋና ግቡ፤ አመስግኑት፥ ስሙንም ባርኩ፤መዝሙረ ዳዊት 100፡2-4
ወደ እግዚአብሄር ስንቀርብ እግዚአብሄር በመልካምነቱ እያጠገበን እንደሆነ እውቅና በመስጠት ብቻ መሆን ይኖርበታል፡፡ አሁንም በጸሎት ወደፊቱ የቀረብነው አንድ ተጨማሪ ነገር እንዲያደርግልን ስለፈለግን እንጂ ከዚህ በፊት እድርጎልን እንደማያውቅ በማጉረምረም መሆን የለበትም፡፡ አንተ ግን ለእኔ የማታደርገው ለምንድነው? በሚል በማጉረምረም በትእቢት ልብ ወደፊቱ ለመቅረብ ከሞከርን ከእግዚአብሄር መልስን የሚያመጣ ጸሎት መፀለይ እንችልም፡፡
ከፀለይን በኋላም እግዚአብሄርን በማመስገን መቀጠል አለብን፡፡ በእምነት የፀለይነው ፀሎት እንደተቀበልን ካመንን ከማመስገን ውጭ ሌላ ምንም ነገር ሊመጣልን አይችለም፡፡ ከፀለይን በኋላ ሁኔታው ሙሉ በሙሉ በተፈጥሮአዊ አለም ተፈጽሞ በህይወታችን እስክናይ ድረስ በማመስገን መቀጠል አለብን፡፡
ስለዚህ እላችኋለሁ፥ የጸለያችሁትን የለመናችሁትንም ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ፥ ይሆንላችሁማል። የማርቆስ ወንጌል 11፡24
ከመፀለያችን በፊትም ከፀለይን በኋላም ያለን የምስጋና ልብ ከእግዚአብሄር ጋር ያለንን ጤናማ ግንኙነት ያሳያል፡፡ ከመፀለያችን በፊትም ከፀለይን በኋላም ያለን የምስጋና ልብ በእግዚአብሄር ፊት የጸለይነው ፀሎት እንዲመለስ ያደርጋል፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
Wednesday, January 11, 2023
Friday, January 6, 2023
Subscribe to:
Posts (Atom)