I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
በክርስትና ለቤተክርስቶን ከተሰጡ አገልግሎቶች መካከል ትንቢት አንዱ ነው፡፡ ትንቢት የሚመጣው ለማነጽና ለመምከር ለማጽናናትም ነው፡፡ ትንቢትን የሚናገር ግን ለማነጽና ለመምከር ለማጽናናትም ለሰው ይናገራል። 1...
-
Then Peter opened his mouth, and said, Of a truth I perceive that God is no respecter of persons: Acts 10:34 God isn’t a respecter...
-
እንደ ፍቅር በጣም አስፈላጊ ነገር የለም፡፡ እንደ ፍቅር ደግሞ ትርጉሙ የተዛባ ነገር በአለም ላይ ምንም ነገር የለም፡፡ ብዙ ጊዜ ሰዎች ፍቅር የሚሉት ምኞታቸውን ነው፡፡ የፍቅርንና የምኞትን ባህሪያት ከእግዚአብሄር ቃ...
-
ነገርን ሁሉ በጊዜው ውብ አድርጎ ሠራው፤ ለሁሉ ዘመን አለው፥ ከሰማይ በታችም ለሆነ ነገር ሁሉ ጊዜ አለው። መክብብ 3፡11 ፣ 1 ምንም ነገር ውብ የመሆን እምቅ ጉልበት ቢኖረውም በእርግጥ ውብ የሚሆነው በራሱ ...
-
እግዚአብሄር ሰውን የፈጠረው ከእርሱ ጋር ህብረት ማድረግ ፈልጎ ነው፡፡ እግዚአብሄር ሰውን በመልኩና በአምሳሉ የፈጠረው ህብረታቸው የተሳካ እንዲሆን ነው፡፡ ሰው በሃጢያት ከመውደቁ በፊት ከእግዚአብሄ ጋር የተሳካ ህብ...
-
ክርስትያን በተለያየ ምክኒያት ከትውልድ ሃገሩ ወጥቶ በሌላ ሃገር ይኖራል፡፡እግዚአብሄር ከአንድ ቦታ ይልቅ በሌላ ቦታ እንድናገለግለው እርሱን እያሳየን አንድንኖር ሲፈልግ በሮችን ይከፍታል፡፡ ራሳችንን ለጌታ...
-
We all come across disappointments. We may face situations that we have never dreamed of facing them one day. We may face something we t...
-
We want God to use us mightily. We ask God “use me and I will do whatever it takes”. When the time to pay the price that isn’t expected...
-
ሰዎችን የሚማርኳቸውና የሚደሰቱባቸው ብዙ ነገሮች አሉ፡፡ ካለ እምነት ግን እግዚአብሄርን ደስ ማሰኘት አይቻልም፡፡ ያለ እምነትም ደስ ማሰኘት አይቻልም፤ ወደ እግዚአብሔር የሚደርስ ...
Tuesday, January 31, 2023
Wednesday, January 25, 2023
Thursday, January 19, 2023
Wednesday, January 18, 2023
Tuesday, January 17, 2023
አሕዛብ ለምን ያጕረመርማሉ? ወገኖችስ ለምን ከንቱን ይናገራሉ? የምድር ነገሥታት ተነሡ፥ አለቆችም በእግዚአብሔርና በመሢሑ ላይ እንዲህ ሲሉ ተማከሩ። ማሰርያቸውን እንበጥስ፥ ገመዳቸውንም ከእኛ እንጣል። በሰማይ የሚኖር እርሱ ይሥቃል፥ ጌታም ይሣለቅባቸዋል። በዚያን ጊዜ በቍጣው ይናገራቸዋል፥ በመዓቱም ያውካቸዋል። መዝሙር 2:1-5
አሕዛብ ለምን ያጕረመርማሉ? ወገኖችስ ለምን ከንቱን ይናገራሉ? የምድር ነገሥታት ተነሡ፥አለቆችም በእግዚአብሔርና በመሢሑ ላይ እንዲህ ሲሉ ተማከሩ። ማሰርያቸውን እንበጥስ፥ገመዳቸውንም ከእኛ እንጣል። በሰማይ የሚኖር እርሱ ይሥቃል፥ ጌታም ይሣለቅባቸዋል። በዚያን ጊዜበቍጣው ይናገራቸዋል፥ በመዓቱም ያውካቸዋል። መዝሙር 2:1-5
Sunday, January 15, 2023
የሁለቱ ቅርጫቶች ወግ
አንድ ልቤን የነካኝን ታሪክ ልንገራችሁ፡፡
እግዚአብሄር ለአንድ አገልጋይ ስለአንዲት የምትፀልይ ሴት ራእይ አሳየው፡፡ በራእዩ ውስጥ ሁለት ቅርጫቶችን ያያል፡፡ አንዱ ቅርጫት ሙሉ ነው አንዱ ቅርጫት ግን ውስጡ ያለበት ነገር እጅግ በጣም ትንሽ ነው፡፡ እግዚአብሄርን ይህ ምንድነው ? ብሎ ስለትርጉሙ ሲጠይቅ ስለሁለቱ ቅርጫቶች እንዲህ ሲል ተናገረው፡፡ እነዚህ ቅርጫቶች የዚህች ሴት የፀሎት እና የምስጋና ህይወትዋ ምሳሌዎች ናቸው፡፡ ይህች ሴት መፀለይ ታውቃለች፡፡ ካለማቋረጥ አብዝታ ትፀልያለች ትጮኻለች፡፡ ይህ የምትመለከተው ሙሉው ጭርጫት የፀሎት ህይወቷ ነው፡፡ ይህ የምትመለከተው እጅግ በጣም ትንሽ ነገር ያለበት ቅርጫት ደግሞ የምስጋና ህይወቷ ነው፡፡ ይህች ሴት መፀለይ ታውቃለች እንጂ ማመስገን አታውቅም፡፡ ስለዚህ ፀሎትዋ እንደሚገባው ውጤታማ አይደለም፡፡
ይህች ሴት ማመስገን ስትጀምር እና የምስጋና ቅርጫትዋ እየሞላ ሲደሄድ የፀለየችው ፀሎትዋ እየተመለሰ ይሄዳል ብሎ እግዚአብሄር አስረዳው፡፡
ይግህ ታሪክ ስለ እያንዳንዳችን የፀሎት ህይወት ወሳኝ ነገርን ያስተምረናል፡፡
ሰው መፀለዩን እንጂ እንዴት በምስጋና ልብ መፀለይ እንዳለበት ካላወቀ በፀሎት ህይወቱ ውጤታማ ሊሆን አይችልም፡፡ ከፀለየ በኋላ እንዴት በማመስገን መቀጠል እንዳለበት የማይረዳ ሰው ፀሎቱ ፍሬያማ መሆን አይችልም፡፡
ከእግዚአብሄር ጋር ያለን ማንኛውም ግንኙነት በምስጋና ልብ መሆን አለበት፡፡ በአጠቃላይ ከእግዚአብሄር ጋር ያለን ግንኙነት በትህትና ለእግዚአብሄር አምላክነት እና መልካምነት እውቅና በመስጠት ካልሆነ ውጤታማ አይሆንም፡፡
በፀሎትም ወደ እግዚአብሄር መቅረብ የህይወታችን እረኛ እንደሆነ ፣ የሚያሳጣን እንደሌለ ፣ በእርሱ አቅርቦት በየእለቱ እንደምንኖር እውቅና መስጠት ይጠይቃል፡፡ ወደ እግዚአብሄር ስንቀርብ በማጉረምረም መሆን የለበትም፡፡ ወይም ደግሞ እግዚአብሄር በትክከል እንዳልያዘን ፣ ምንምም ነገር አድርጎን እንደማያውቅ መቅረብ የለብንም፡፡ ወደ እግዚአብሄር ስንቀርብ ለመጀመሪያ ጊዜ አንድ ነገር ሊያደርግልን እንደሆነ በማንጎራጎር ከሆነ ለአምላክነቱ የሚገባውን እውቅና ስላልሰጠ በፀሎታችን እግዚአብሄር ደስ አይሰኝም፡፡
በደስታም ለእግዚአብሔር ተገዙ፥ በሐሤትም ወደ ፊቱ ግቡ። እግዚአብሔር እርሱ አምላክ እንደ ሆነ እወቁ፤ እርሱ ሠራን እኛም አይደለንም፤ እኛስ ሕዝቡ የማሰማርያውም በጎች ነን። ወደ ደጆቹ በመገዛት፥ ወደ አደባባዮቹም በምስጋና ግቡ፤ አመስግኑት፥ ስሙንም ባርኩ፤መዝሙረ ዳዊት 100፡2-4
ወደ እግዚአብሄር ስንቀርብ እግዚአብሄር በመልካምነቱ እያጠገበን እንደሆነ እውቅና በመስጠት ብቻ መሆን ይኖርበታል፡፡ አሁንም በጸሎት ወደፊቱ የቀረብነው አንድ ተጨማሪ ነገር እንዲያደርግልን ስለፈለግን እንጂ ከዚህ በፊት እድርጎልን እንደማያውቅ በማጉረምረም መሆን የለበትም፡፡ አንተ ግን ለእኔ የማታደርገው ለምንድነው? በሚል በማጉረምረም በትእቢት ልብ ወደፊቱ ለመቅረብ ከሞከርን ከእግዚአብሄር መልስን የሚያመጣ ጸሎት መፀለይ እንችልም፡፡
ከፀለይን በኋላም እግዚአብሄርን በማመስገን መቀጠል አለብን፡፡ በእምነት የፀለይነው ፀሎት እንደተቀበልን ካመንን ከማመስገን ውጭ ሌላ ምንም ነገር ሊመጣልን አይችለም፡፡ ከፀለይን በኋላ ሁኔታው ሙሉ በሙሉ በተፈጥሮአዊ አለም ተፈጽሞ በህይወታችን እስክናይ ድረስ በማመስገን መቀጠል አለብን፡፡
ስለዚህ እላችኋለሁ፥ የጸለያችሁትን የለመናችሁትንም ሁሉ እንዳገኛችሁት እመኑ፥ ይሆንላችሁማል። የማርቆስ ወንጌል 11፡24
ከመፀለያችን በፊትም ከፀለይን በኋላም ያለን የምስጋና ልብ ከእግዚአብሄር ጋር ያለንን ጤናማ ግንኙነት ያሳያል፡፡ ከመፀለያችን በፊትም ከፀለይን በኋላም ያለን የምስጋና ልብ በእግዚአብሄር ፊት የጸለይነው ፀሎት እንዲመለስ ያደርጋል፡፡
አቢይ ዋቁማ ዲንሳ Abiy Wakuma Dinsa
Wednesday, January 11, 2023
Friday, January 6, 2023
Subscribe to:
Comments (Atom)






