I am a born again christian passionate to teach the word of God in simplicity.
Popular Posts
-
ኢየሱስ ለእኛ ሰው ሆኖ ወደምርድ ስለመጣ ፍፁም ምሳሌያችን ነው፡፡ ማንንም ባንከተል ኢየሱስን መከተል አለብን፡፡ ማንም ምንም የሚጎድለው ባህሪ ቢኖር ኢየሱስ በባህሪው ፍፁም ነው፡፡ ኢየሱስ ሙሉ ለሙሉ ልንከተለው የምንች...
-
በገዛ ሥጋው የሚዘራ ከሥጋ መበስበስን ያጭዳልና፥ በመንፈስ ግን የሚዘራው ከመንፈስ የዘላለምን ሕይወት ያጭዳል። ወደ ገላትያ ሰዎች 6፡8 የሥጋ ሥራም የተገለጠ ነው እርሱም ዝሙት፥ ርኵ...
-
ዳሩ ግን፥ ወንድሞች ሆይ፥ ይህን እናገራለሁ፤ ዘመኑ አጭር ሆኖአል፤ ከእንግዲህ ወዲህ ሚስቶች ያሉአቸው እንደሌላቸው ይሁኑ፥ 1 ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 7 ፡ 29 የትዳር አላማ አንዱ ...
-
ሳሙኤልም፦ በውኑ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ደስ እንደሚለው እግዚአብሔር በሚቃጠልና በሚታረድ መሥዋዕት ደስ ይለዋልን? እነሆ፥ መታዘዝ ከመሥዋዕት፥ ማዳመጥም የአውራ በግ ስብ ከማቅረብ ይበልጣል። ዓመፀኝነት እንደ ...
-
የሰይጣን አላማው መስረቅ ማረድና ማጥፋት ነው፡፡ ሰይጣን ከመስረቅ ከማረድና ከማጥፋት ውጭ ሌላ ምንም አላማ የለውም፡፡ ሌባው ሊሰርቅና ሊያርድ ሊያጠፋም እንጂ ስለ ሌላ አይመጣም፤ የዮሐንስ ወንጌል 10፡1...
-
እግዚአብሄር የአላማ አምላክ ነው፡፡ እግዚአብሄር የፈጠረን ለክብሩ ነው፡፡ የፈጠረን እግዚአብሄር በህይወታችን ምን እንደምንሰራ ግድ ይለዋል፡ ፡ እግዚአብሄር ምን እንደምንሰራ ግድ እንደሚለው ሁሉ ለምን ምክኒያት እንደም...
-
ሳሙኤልም፦ በውኑ የእግዚአብሔርን ቃል በመስማት ደስ እንደሚለው እግዚአብሔር በሚቃጠልና በሚታረድ መሥዋዕት ደስ ይለዋልን ? እነሆ፥ መታዘዝ ከመሥዋዕት፥ ማዳመጥም የአውራ በግ ስብ ከማቅረብ...
-
እኛ በክርስቶስ ኢየሱስ አዳኝነት አምነን የዳንን ሁላችን እግዚአብሄር በምድር ላይ ለሰጠን የቤት ስራ በእግዚአብሄር መንፈስ ተቀብተናል፡፡ ካለ እግዚአብሄር መንፈስ እርዳታ የእግዚአብሄርን ስራ መስራት አይቻልም፡፡ የእ...
Sunday, July 31, 2022
Saturday, July 30, 2022
Thursday, July 28, 2022
Monday, July 25, 2022
ባለ ጠጋም በውርደቱ ይመካ
የተዋረደው ወንድም ግን በከፍታው፥ ባለ ጠጋም በውርደቱ ይመካ፤ እንደ ሣር አበባ ያልፋልና። ፀሐይ ከትኵሳት ጋር ይወጣልና፥ ሣርንም ያጠወልጋልና፥ አበባውም ይረግፋልና፥ የመልኩም ውበት ይጠፋልና፤ እንዲሁ ደግሞ ባለ ጠጋው በመንገዱ ይዝላል። የያዕቆብ መልእክት 1:9-11
ሁላችንም
በህይወታችን
ከእኛ
የሚበልጥ
የሚያስመካ
ሃያል
ነገርን
እንፈልጋለን፡፡
ነገር
ግን
ያስመካል
ብለን
የምናስበው
ነገር
ሁሉ
የሚያስመካ
አይደለም፡፡
መፅሃፍ
ቅዱስ
በሚታይ
ነገር
የተዋረደ
ወንድም
ሊዋረድ
እንደማይገባው
ያስተምረናል፡፡
በምድራዊ
ነገር
ብዙ
ነገር
የሌለው
ሰው
በውርደቱ
እንዳይዋረድ
መፅሃፍ
ቅዱስ
ያስጠነቅቃል፡፡
በምድራዊ
ህይወት
ደረጃው
ዝቅተኛ
የሆነ
ሰው
ውርደቱን
በሚሸፍን
በእግዚአብሄር
እንዲመካ
ያስተምራል፡፡
በምድራዊ
ነገር
ባለጠጋ
መሆን
ለመመካት
ብቁ
ያልሆነ
ነገር
በመሆኑ
በምድራዊ
ነገር
ባለጠጋ
የሆነ
ሰው
በባለጠግነቱ
እንዳይመካ
መፅሃፍ
ቅዱስ
ይመክራል፡፡
ባለጠጋ
መመካት
ያለበት
የሚያስፈልገውን
በማያጎድልበት
በእግዚአብሄር
ብቻ
ነው፡፡
የእግዚአብሄር
ነገር
ብቻ
እንጂ
በምድር
ላይ
ምንም
የሚያስተማምን
ምንም
ቋሚ
ነገር
የለም፡፡
ብላቴኖች
ይደክማሉ
ይታክቱማል፥
ጐበዛዝቱም
ፈጽሞ
ይወድቃሉ፤
እግዚአብሔርን
በመተማመን
የሚጠባበቁ
ግን
ኃይላቸውን
ያድሳሉ፤
እንደ
ንስር
በክንፍ
ይወጣሉ፤
ይሮጣሉ፥
አይታክቱም፤
ይሄዳሉ፥
አይደክሙም።
ኢሳያስ
40፡30-31
Saturday, July 23, 2022
ስለገንዘብ የመመካት ስጋዊነት
ስለገንዘብ የመመካት ስጋዊነት
ዓለምን ወይም በዓለም ያሉትን አትውደዱ፤ በዓለም ያለው ሁሉ እርሱም የሥጋ ምኞትና የዓይን አምሮት ስለገንዘብም መመካት ከዓለም ስለ ሆነ እንጂ ከአባት ስላልሆነ፥ ማንም ዓለምን ቢወድ የአባት ፍቅር በእርሱ ውስጥየለም። 1 ኛ ዮሀንስ 3:15-16
ስለገንዘብ የመመካት ስጋዊነት ከህፃንነት የሚመነጭ የስጋዊነት ሀጢያት ነው::
ስለገንዘብ የመመካት ስጋዊነት የእግዚአብሔርን ፍቅር በአግባቡ ካለመረዳት የሚመጣ አለመብሰል እንጭጭነትነው::
ሰው በእግዚአብሐር የተወደደበትን ጥልቅ ፍቅር ሲረዳ የገንዘብን ትንሽነት እና ውስንነት ስለሚረዳ በገንዘብውይም በኑሮ ከመመካት የስጋዊነት ሀጢያት ይድናል::
ከክፉ የሚጠብቀውን የሚያኖረውን የእግዚአብሔርን ፍቅር በሚገባ የተረዳ ሰው ስለገንዘብ መመካትያሳፍረዋል::
እግዚአብሔር እንዲህ ይላል። ጠቢብ በጥበቡ አይመካ፥ ኃያልም በኃይሉ አይመካ፥ ባለ ጠጋም በብልጥግናውአይመካ፤ ነገር ግን የሚመካው። ምሕረትንና ፍርድን ጽድቅንም በምድር ላይ የማደርግ እኔ እግዚአብሔር መሆኔንበማወቁና በማስተዋሉ በዚህ ይመካ፤ ደስ የሚያሰኙኝ እነዚህ ናቸውና፥ ይላል እግዚአብሔር። ኤርሚያስ 9:23-24
ሰው በሚበላው ምግብ ውድነት ከተመካ ስጋዊ ሰው ነው::
ሰው በሚነዳው መኪና ውድነት ከተመካ ስጋዊ ሰው ነው እንጂ መንፈሳዊ ሰው አይደለም::
ሰው ባለመማሩ ካዘነ እና ከተዋረደ መንፈሳዊ ስው አይደለም ማለት ነው::
ሰው ባለው እውቀት ከተመካ ከአለማዊ አስተሳሰብ ያልዳነ ስጋዊ ሰው ነው::
ሰው ባለው ሀብት ከተመካ ስጋዊ ሰው ነው::
ሰው ባለው ዘመድ ከተመካ ስጋዊ ሰው ነው::
ሰው በሚለብሰው ልብስ ውድነት ከተመካ መንፈሳዊ ሰው አይደለም::
ሰው በእግዚአብሔር ሳይሆን በውበቱ ከተመካ እን ደስ ድስ ከተሰኘ ስጋዊ ሰው ነው::
ሰው በድህነቱ ካዘነ እና ከተዋረደ መንፈሳዊ ስው አይደለም ማለት ነው::
በሚኖርበት ቤት ትልቅነት እና ውድነት የሚመካ ሰው መንፈሳዊ አይደለም ማለት ነው::