Popular Posts

Wednesday, November 30, 2016

ኤጭ ደግሞ ለኑሮ

እንግዲህ፦ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ማቴዎስ 6፡31-32
ኢየሱስን የምንከተል ሁላችን ለኑሮ እንዳንጨነቅ ኢየሱስ ደጋግሞ ደጋግሞ ያስተምረናል፡፡ ስለኑሮ መጨነቅ የእናንተ አይደለም እያለን ነው፡፡ ለኑሮ መጨነቅ አይመጥናችሁም እያለን ነው፡፡ ስለኑሮ መጨነቅ ክብራችሁ አይፈቅደውም እያለንም ነው፡፡
ስለኑሮ መጨነቅንና ለመኖር መኖርን እንደትልቅ ነገር አይተውት የሚኖሩለትና የሚሞቱለት ሰዎች አሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች ለመኖር ነው የሚኖሩትና የሚሰሩት፡፡ እነዚህ ሰዎች ለመኖር የማያደርጉት ነገር የለም፡፡ ከመኖር ውጭ የሚኖሩለት ምንም ነገር የላቸውም፡፡ እነዚህ ሰዎች መኖር የሙሉ ጊዜ ሃላፊነት ነው፡፡
ህይወታቸውን ሁሉ የሰጡት ለመኖር የሚያስፈልገውን በማሟላት ነው፡፡ የሚኖሩለት የእግዚአብሄር ጥሪ በህይወታቸው ላይ የለም፡፡ እግዚአብሄር ለህይወታቸው ያስቀመጠውን የተለየ አላማ አላገኙትም፡፡ ስለሚበላና ስለሚለበስ ከመጨነቅ የተሻለ ስራ የላቸውም፡፡
ስለኑሮ መጨነቅ እግዚአብሄርን የማያውቁ የተሻለ የህይወት አላማ የሌላቸው ሰዎች የህይወት ዘይቤ እንደሆነ ኢየሱስ ያስተምራል፡፡ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ማቴዎስ 6፡32
ለመኖር የሚጨነቁት ሌላ ምንም ሃላፊነት የሌለባቸው ሰዎች ናቸው፡፡ ለመኖር የሚጨነቁት ሌላ የተሻለ የሚኖሩለት የህይወት ራእይ ስለሌላቸው ነው፡፡ ለመኖር የሚጨነቁት በህይወታቸው የሚከተሉት የእግዚአብሄር አላማ በህይወታቸው የሌላቸው ናቸው፡፡ እነዚያ ለመኖር የሚጨነቁት መንገዱ የጠፋባቸውና እግዚአብሄር ለከበረ የህይወት አላማ እግዚአብሄርን ለማምለክና ለማገልገል እንደጠራቸው የማያውቁ ናቸው፡፡ ስለኑሮ የሚጨነቁት የሚፈልጉት የእግዚአብሄር መንግስት ስሌላቸው ነው፡፡ እነዚህ ስለሚበላና ስለሚጠጣ የሚጨነቁት የሚፈልጉት የእግዚአብሄር ፅድቅ ስለሌላቸው ነው፡፡
ነገር ግን አስቀድማችሁ የእግዚአብሔርን መንግሥት ጽድቁንም ፈልጉ፥ ይህም ሁሉ ይጨመርላችኋል። ማቴዎስ 6፡33
ኑሮን ዋና የህይወት አላማ ያደረጉት ናቸው ስለመኖር ብለው የሚኖሩት፡፡ እነዚህ ሰዎች ህይወታቸውን ሁሉ የሚጨርሱት ለመኖር በመጨነቅ ለመኖር በመሞከር ብቻ ነው፡፡ እንደው ከመኖር የተሻለ ምንም የሚከተሉት የህይወት አላማ የላቸውም፡፡ የመጨረሻውና ታላቁ ግባቸው መኖር ነው፡፡
በዚች ሕይወት ብቻ ክርስቶስን ተስፋ ያደረግን ከሆነ፥ ከሰው ሁሉ ይልቅ ምስኪኖች ነን። 1ኛ ቆሮንቶስ 15፡19
ለእነርሱ መኖር ብቻውን ትልቅ ነገር ነው፡፡ ለእነርሱ እግዚአብሄር ሊሰሩት ያዘጋጀውን መልካሙን ስራ መስራት ሳይሆን ኖሮ ኖሮ መሞት ትልቅ ገድል ነው፡፡
እኛ ፍጥረቱ ነንና፤ እንመላለስበት ዘንድ እግዚአብሔር አስቀድሞ ያዘጋጀውን መልካሙን ሥራ ለማድረግ በክርስቶስ ኢየሱስ ተፈጠርን። ኤፌሶን 2፡10
ኢየሱስ ስለኑሮ አትኑሩ ለመንግስቴ ኑሩ እያለን ነው፡፡ ፅድቅን ለማሳየት ስትኖሩ ይህ ሁሉ ነገር ምርቃት ነው እያለን ነው፡፡
እንግዲህ፦ ምን እንበላለን? ምንስ እንጠጣለን? ምንስ እንለብሳለን? ብላችሁ አትጨነቁ፤ ይህንስ ሁሉ አሕዛብ ይፈልጋሉ፤ ይህ ሁሉ እንዲያስፈልጋችሁ የሰማዩ አባታችሁ ያውቃልና። ማቴዎስ 6፡31-32
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
#ኢየሱስ #ጌታ #ራእይ #ህልም #አላማ #መሰረታዊፍላጎት #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ጥሪ #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Friday, November 25, 2016

ካለ ንግግር ማመስገኛ መንገዶች

እግዚአብሄርን ማመስገን በአፍ እግዚአብሄር ሆይ አመሰግንሃልሁ ከማለት ያለፈ ነው፡፡
ለእግዚአብሄር መስእት ያመጡ ሰዎች በእግዚአብሄር ተገስፀዋል፡፡ የምስጋናን መስዋእት እንዲያመጡ እግዚአብሄር አዞዋል፡፡ በመኝሃፍ ቅዱስ ካለቃልና ካለንግግር ቀን ለቀን የእግዚአበሄርን ክብር እንደሚናገሩ ያስተምራል፡፡
ሰማያት የእግዚአብሔርን ክብር ይናገራሉ፥ የሰማይም ጠፈር የእጁን ሥራ ያወራል። ቀን ለቀን ነገርን ታወጣለች፥ ሌሊትም ለሌሊት እውቀትን ትናገራለች። ነገር የለም መናገርም የለም፥ ድምፃቸውም አይሰማም። ድምፃቸው ወደ ምድር ሁሉ፥ ቃላቸውም እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ። መዝሙር 19፡1-4
እግዚአብሄርን በቃላችን አመስግነን አንጠግብም፡፡ እግዚአብሄር ካደረገልን አንፃር የእግዚአብሄርን ውለታ በምንም አንከፍለውም፡፡ ከንግግር ውጭ ግን እግዚአብሄርን አመሰግንሃልሁ የምንልበት ሌሎች መንገዶች አሉ፡፡ ከንግግር ያለፈ በእያንዳንዱ አስተሳሰባችንና አካሄዳችን እግዚአብሄርን ለማመስገን እድሉ ተሰጥቶናል፡፡ ካለንግግር እግዚአብሄርን የምናመሰግንበት ሰባቱ የህይወት ዘይቤዎች
  • · ለሰዎች በጎን ማድረግ
ከእግዚአብሄር መልካምነት የተቀበለ ሰው ሁሉ በተራው ለሰዎች መልካም በማድረግ እግዚአብሄርን በተዘዋዋሪም አመሰግናለሁ ይለዋል፡፡ መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ። ማቴዎስ 5፡16
  • · ሰዎችን ይቅር ማለት
እግዚአብሄር እርሱን ይቅር እንዳለው የተረዳና አመሰግናለሁ የሚል ሰው በተራው ይቅርታ የሚፈልግ ሰው ሲያገኝ ይቅር በማለት ካለንግግር እግዚአብሄርን በድርጊቱ ያመሰግናል፡፡ ብዙም ከተሰጠው ሰው ሁሉ ከእርሱ ብዙ ይፈለግበታል፥ ብዙ አደራም ከተሰጠው ከእርሱ አብዝተው ይሹበታል።ሉቃስ 12፡48 ከዚያ ወዲያ ጌታው ጠርቶ፦ አንተ ክፉ ባሪያ፥ ስለ ለመንኸኝ ያን ዕዳ ሁሉ ተውሁልህ፤ እኔ እንደ ማርሁህ ባልንጀራህ የሆነውን ያን ባሪያ ልትምረው ለአንተስ አይገባህምን? አለው። ማቴዎስ 18፡32-33
  • · እግዚአብሄርን መታዘዘ
እግዚአብሄርን በንግግር ብቻ ማመስገን ፈፅሞ አያረካንም ፡፡ እግዚአብሄርን የምናመሰግንበት ሌላው መንገድ እግዚአብሄር እንዳስደሰተን እርሱን በመታዘዝ ማስደሰት ነው፡፡ በጌታ እንደረካንና ደስ እንደተሰኘን ማሳያው መንገድ ቃሉን በመታዘዝ በድርጊት ስናመሰግነው ነው፡፡ ኢየሱስም መለሰ አለውም፦ የሚወደኝ ቢኖር ቃሌን ይጠብቃል፤ አባቴም ይወደዋል ወደ እርሱም እንመጣለን በእርሱም ዘንድ መኖሪያ እናደርጋለን። ዮሃንስ 14፡23
  • · አለማጉረምረም
ህይወቱ እግዚአብሄርን የሚያመሰገን ሰው በንግግሩ እግዚአብሄርን ማመስገን ብቻ ሳይሆን በሚያልፍበት በማንኛውም መንገድ እግዚአብሄር ላይ አያጉረመርምም፡፡ የምትባረክ ነፍስ ትጠግባለች፥ የረካም እርሱ ደግሞ ይረካል። ምሳሌ 11፥25 ደስ ያላት ልብ መልካም መድኃኒት ናት፤ ያዘነች ነፍስ ግን አጥንትን ታደርቃለች። ምሳሌ 17፡22
  • · ራስን ማዋረድና ወይም ትህትና
የሚያመሰግን ልብ ሁል ጊዜ ራሱን ለማዋረድ ዝግጁ ነው፡፡ የሚያመሰግን ልብ ያለው ሰው ሌሎች ሊሰሩት የማይፈቅዱትን ዝቅ ያለውን ነገር ያደረጋል፡፡ የምስጋና ህይወት ያለው ሰው ራሱን ከዝቅተኛ ሰዎች ጋር ሲያስተባብር ይታያል፡፡ እርስ በርሳችሁ በመስማማት ኑሩ። ዝቅተኛ ኑሮ ውስጥ ካሉ ጋር አብራችሁ ለመሆን ፍቀዱ እንጂ አትኵራሩ፤ በራሳችሁም አትመኩ። ሮሜ 12፡16 (መደበኛ ትርጉም)
  • · በአስተሳሰብ ህይወታችን እግዚአብሄርን መፍራት
እግዚአብሄርን የምናመሰግን ከሆነ የእግዚአብሄር ያልሆኑትን ሃሳቦች እንጠየፋቸዋለን፡፡ የሚያመሰግን ልብ ካለን የእግዚአብሄርንና የእኛ ጠላት የሆነውን የሰይጣንን ሃሳብ አናስተናግድም፡፡ ምስጉን ነው በክፉዎች ምክር ያልሄደ፥ በኃጢአተኞችም መንገድ ያልቆመ፥ በዋዘኞችም ወንበር ያልተቀመጠ። ነገር ግን በእግዚአብሔር ሕግ ደስ ይለዋል፥ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል። መዝሙር 1፡1-2
  • እግዚአብሄርን መፈለግ
ለእግዚአብሄር በምስጋና የተሞላ ልብ ያለው ሰው ሁል ጊዜ እግዚአብሄርን በሁሉም የህይወት ክፍሉ ይፈልጋል፡፡ እግዚአብሔርን አመስግኑ ስሙንም ጥሩ፥ ለአሕዛብም ሥራውን አውሩ። ተቀኙለት፥ ዘምሩለት፥ ተአምራቱንም ሁሉ ተናገሩ። በቅዱስ ስሙ ተጓደዱ፤ እግዚአብሔርን የሚፈልግ ልብ ደስ ይበለው። እግዚአብሔርን ፈልጉት ትጸናላችሁም፤ ሁልጊዜ ፊቱን ፈልጉ። መዝሙር 105፡1-4
ይህንን ፅሁፍ ሼር ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ምስጋና #እምነት #መደገፍ #ልብ #ቃል #ምስጉን #ሃሳብ #ማሰላሰል #ወንጌል #ደቀመዝሙር #ኢየሱስ #ጌታ #መዳን #አማርኛ #ኢትዮጲያ #አቢይዋቁማ #ፌስቡክ #አዋጅ

10 Reasons Why Every Day is a Thanksgiving Day?

It is very wise to seize any opportunity set-aside to give thanks to the Lord.  But thanks-giving isn’t a once a year activity to be observed. There are good reasons that every day must be a thanksgiving day.
There are valid reasons that in everything we give thanks to the Lord and there are enough reasons that God deserves our thank you in each and every moment of our lives. We make a big mistake if we forget to thank him for everything he is doing in our lives, and it will be equally wrong if we stop thanking him or murmur against him for any reason. 
Thanksgiving should be a day-to-day attitude towards God. Whatever we do we have to do it recognizing his goodness in our lives. Any day in which we don’t actively praise the Lord is a waste of time. 
  • · God is good all the time 
The Lord is good, a refuge in times of trouble. He cares for those who trust in him, Nahum 1:7
  • · His compassion is new every day
Because of the LORD's great love we are not consumed, for his compassions never fail. They are new every morning; great is your faithfulness. Lamentations 3:22-23
  • God personally sustains us.
We could never sustain ourselves. I lie down and sleep; I wake again, because the Lord sustains me. Psalm 3:5
  • God deserves our praise as He holds our breath we live and we have our being in him
For in him we live and move and have our being.' As some of your own poets have said, 'We are his offspring.' Acts 17:28
  • We have to use every day every day for He loved and saved us while we were yet sinners and his enemies. he saved us, not because of righteous things we had done, but because of his mercy.
He saved us through the washing of rebirth and renewal by the Holy Spirit, Titus 3:5
  • · God deserves our thank you as he provides our needs each day. 
And my God will meet all your needs according to the riches of his glory in Christ Jesus. Philippians 4:19
  • · The fact we have breath reminds us to praise the Lord.
Let everything that has breath praise the LORD. Praise the LORD. Psalm 150:6
  • · Everyday is a thanksgiving day as God is our light and fortress that we shall not fear anyone or anything.
Of David. The LORD is my light and my salvation-- whom shall I fear? The LORD is the stronghold of my life-- of whom shall I be afraid? Psalm 27:1
  • · We are grateful every day as our gratefulness attitude is the way we acknowledge his goodness. 
What shall I return to the LORD for all his goodness to me? Psalm 116:12
  • · We can’t have any valid reason to be ungrateful.
God isn’t only He loves us he is also loved. He can’t be anything else except love. In whatever way you look at God he is love and nothing else.
 His mouth is sweetness itself; he is altogether lovely. This is my beloved, this is my friend, daughters of Jerusalem. Song of Solomon 5:16
Whoever does not love does not know God, because God is love. 1 John 4:8

#God #Jesus #knowledge #rejoice #trustgod #grace #salvation #church #testimony #rejoice #preaching #Bible #theword #Abiydinsa #scriptures #abiywakumadinsa

Wednesday, November 23, 2016

የአቋም መግለጫ

እኔ እግዚአብሔር ነኝ ስሜ ይህ ነው፤ ክብሬን ለሌላ፥ ምስጋናዬንም ለተቀረጹ ምስሎች አልሰጥም። ኢሳይያስ 42:8
እግዚአብሄር እንዲህ ይላል ክብሬን ለሌላ ምስጋናዬን ለተቀረፁ ምስሎች አልሰጥም፡፡ እግዚአብሄር ፡፡ ምንም ክርክር እንዳይነሳ እኔ እግዚአብሄር ነኝ ስሜም ይህ ነው በማለት በመጀመሪያ ስሙን ግልፅ አደረገልን፡፡
በሁለተኛ ደረጃ ክብሩን ለማንም ለማንም እንደማይሰጥ ተናገረ፡፡ ብዙ የሚያጋራው ነገሮች ቢኖሩም ክብሩን ግን ለማንም አይሰጥም፡፡ ከማንም ሰው ጋር እኩል መቆጠር አይፈልግም፡፡
ማንም የሰው ልጅ የእግዚአብሄርን ክብሩን እንዲሸፍን አይፈቅድም፡፡
የእግዚአብሄርን ክብር መውሰድ የስነመለኮት አመለካከት ብቻ ሳይሆን በሰው ልጅ የእለት ተእለት ህይወት ሊከሰት የሚችል የዘወትር ፈተና ነው፡፡ ሰው ካልተጠነቀቀ የእግዚአብሄን ክብር በመውሰድ እግዚአብሄርን ያስቆጣዋል፡፡ አንዳንደ ሰው እኔ ምን ክብር አለፅ ይላል ነገር ግን ሰዎች አንተን አልፈው እግዚአብሄርን ማየት ካቃታቸው ወድቀሃል፡፡ ለእግዚአብሄር የሚገባውን ትኩረት ራስህ ጋር ካስቀረኸው ክብሩን ወስደሃል፡፡ ሰዎች ወደ አንተ ሲያመለክቱ ወደእግዚአብሄር ካላመለከትክ ክብሩ ጣፍጦሃል ማለት ነው፡፡
ኢየሱስ በምድር ላይ ይመላለስ በነበረ ጊዜ ለእግዚአብሄር የሚገባውን ክብር ወደ እርሱ ሲያመጡ የእግዚአብሄርን ክብር ላለውሰድ ይጠነቀቅ ነበር፡፡
ኢየሱስም፦ ስለ ምን ቸር ትለኛለህ? ከአንዱ ከእግዚአብሔር በቀር ቸር ማንም የለም። ሉቃስ 18፡19
በበርናባስና በጳውሎስ ታዕምራት በተደረገ ጊዜ ሰዎች ሊያመልኳቸው ሲሞክሩ የእግዚአብሄርን ክብር መውሰድ በጣም ስሱና ሴልሲቲቭ ነገር ስለሆነ ወዲያው ነው ፊት ለፊት የተቃወሙት፡፡ ሰዎች እነርሱን ባከበሩዋቸው መጠን ራሳቸውን አዋረዱ፡፡
ሐዋርያት በርናባስና ጳውሎስ ግን ይህን በሰሙ ጊዜ ልብሳቸውን ቀደው ወደ ሕዝቡ መካከል እየጮኹ ሮጡ፥ ሐዋርያት 14፡14
የሰዎች ትኩረት ከእነርሱ ላይ ተነስቶ ወደ እግዚአብሄር እንዳይሄድ የሚፈልጉ ለእግዚአብሄር መሰጠት ያለበትን ክብር በተለያየ ምክኒያት ለራሳቸው የሚወስዱ ሰዎችን እግዚአብሄር ይናገራል ክብሬን ለሌላ ለማንም አልሰጥም፡፡
ካልተጠነቀቅን ደግሞ እግዚአብሄር ክብሩ እንደማይገባን የሚያሳይበትና የሚያስታውስበት የራሱ መንገድ እንዳለው ከናቡከደነፆር ታሪክ ልንማር ይገባል፡፡ ዳንኤል 5፡19-21
ንጉሱ የተናገረውን ንግግር አድምጠው ሰዎች ለእግዚአብሄር የሚገባውን ክብር ለሰው ሰጡ፡፡ ችግሩ ሰው ክብሩን መስጠቱ አይደለም፡፡ ችግሩ ግን የተሰጠውን ክብር ለእግዚአብሄር መልሶ አለመስጠቱ ነው፡፡ ሰው የእግዚአብሄርን ክብር እንዳይሸፍን ራሱን አለመደበቁ ነው ችግሩ ፡፡
ሕዝቡም፦ የእግዚአብሔር ድምፅ ነው የሰውም አይደለም ብለው ጮኹ። ለእግዚአብሔርም ክብር ስላልሰጠ ያን ጊዜ የጌታ መልአክ መታው በትልም ተበልቶ ሞተ። ሐዋርያት 12፡22-23
የእግዚአብሄርን ክብር መውሰድ እኔን አይመለከተኝም የሚል ሰው የለም፡፡ ፍራ እንጂ የትእቢትን ነገር አታስብ፡፡ ራስህን አዋርድ፡፡ ሁልጊዜ ለእግዚአብሄር አምላክነት እውቅና ስጥ፡፡ በምንም ምክኒያት ይሁን የሰዎች ትኩረት አንተ ጋር እንዳይቀር ተጠንቀቅ፡፡ ሰዎች ክብር ሲሰጡህ በተራህ አንተ ለእግዚአብሄር ክብር ስጥ፡፡
እንግዲህ የምትበሉ ወይም የምትጠጡ ብትሆኑ ወይም ማናቸውን ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉት። 1ኛ ቆሮንቶስ 10፡31
ሁሉ ከእርሱና በእርሱ ለእርሱም ነውና፤ ለእርሱ ለዘላለም ክብር ይሁን፤ አሜን። ሮሜ 11፡36
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ኢየሱስ #ጌታ #ክብር #ትእቢት #ኩራት #እግዚአብሄር #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #መዳን #መፅሃፍቅዱስ #ሰላም #አቢይ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ #እወጃ #መናገር #ፅናት #ትግስት #መሪ

Tuesday, November 22, 2016

መዳንህን እርግጠኛ ነህ?

መዳናችንን በእርግጠኝነት የምናውቅው ከስጋ ተለይተን ስንሞት ወይም ኢየሱስ ዳግም ተመልሶ ሲመጣ ነው ወይስ አሁን መዳናችንን ርግጠኛ መሆን እንችላለን የሚሉት ሃሳቦች ሰዎችን ያከራክራሉ፡፡
የእግዚአብሄር ቃል ግን ስለመዳናችን ምን እንደሚል ማወቅ አሁን ስለመዳናችን ምንም ጥርጥር እንዳይኖረንና እንደዳነ ሰው የእግዚአብሄር ልጅነትን ስራ በምድር ላይ ሰርተን እንድናከብረው ያስችለናል፡፡
ኢየሱስ በመስቀል ላይ በእኛ ምትክ ስለሞተና ስለተነሳ ኢየሱስ የሰራውን ስራ በእምነት ለእኔ ነው ብሎ ከመቀበል ወዲያ እኛ ለመዳናችን የምናደርገው ምንም ነገር የለም፡፡ የሚጠበቅንብን የደህንነትን ነፃ ስጦታ በእምነት መቀበል ነው፡፡
• ኢየሱስ በመስቀል ላይ የከፈለልንን የሃጢያት እዳ ለእኔ ነው ብለን ከተቀበልን የዘላለም ህይወት አለን፡፡
ልጁ ያለው ሕይወት አለው፤ የእግዚአብሔር ልጅ የሌለው ሕይወት የለውም። የዘላለም ሕይወት እንዳላችሁ ታውቁ ዘንድ በእግዚአብሔር ልጅ ስም ለምታምኑ ይህን ጽፌላችኋለሁ። 1ኛ ዮሐንስ 5፡12-13
• ኢየሱስ ከዘላለም ፍርድ ሊያድነን እንደ ተላከ የሚያምን ሰው ከሞት ወደ ህይወት ተሸጋግሯል ወደ ፍርድም አይመጣም፡፡
እውነት እውነት እላችኋለሁ፥ ቃሌን የሚሰማ የላከኝንም የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው፥ ከሞትም ወደ ሕይወት ተሻገረ እንጂ ወደ ፍርድ አይመጣም። ዮሐንስ 5፡24
• ለእርሱ የሰጠነውን እንዳንሰናከል ማድረግ ይችላል፡፡ እንዲሁም ነውር የሌለን ሆነን በፊቱ እንድንቆም ማድረግ ይቻለዋል፡፡ ሳትሰናከሉም እንዲጠብቃችሁ፥ በክብሩም ፊት በደስታ ነውር የሌላችሁ አድርጎ እንዲያቆማችሁ ለሚችለው ይሁዳ 1፡24
• ለመዳን ወደ እርሱ ለመጣን ለሁላችን ሊማድልንና ፈፅሞ ሊያድነን ኢየሱስ በህይወት ይኖራል፡፡
ስለ እነርሱም ሊያማልድ ዘወትር በሕይወት ይኖራልና ስለዚህ ደግሞ በእርሱ ወደ እግዚአብሔር የሚመጡትን ፈጽሞ ሊያድናቸው ይችላል። ዕብራውያን 7፡25
• ኢየሱስን አዳኛችንና የህይወታችን ጌታ አድርገን ለተቀበልነው ሁሉ የዘላለም ህይወት ተሰጥቶናል፡፡ ከእግዚአብሄር እጅ ሊነጥቀን የሚችል ሃይል የለም፡፡
እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ ለዘላለምም አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም አይነጥቃቸውም። የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል፥ ከአባቴም እጅ ሊነጥቃቸው ማንም አይችልም። ዮሐንስ 10፡28-29
• የአለም ህዝብ ተሰብስቦ አልዳንክም ቢለን እንኳን የእግዚአብሄር ልጆች መሆናችንን መንፈስ ቅዱስ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል፡፡ የእግዚአብሔር ልጆች መሆናችንን ያ መንፈስ ራሱ ከመንፈሳችን ጋር ይመሰክራል። ሮሜ 8፡16
• የመዳኛውን መንገድ ውስብስብ አይደለም፡፡ የዘላለም ህይወት የማግኛው መንገድ በኢየሱስ ማመን ነው፡፡ እውነት እውነት እላችኋለሁ በእኔ የሚያምን የዘላለም ሕይወት አለው። ዮሃንስ 6፡47
• ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፉ ከመሰከረ እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልቡ ካመነ ሁሉ ይድናል፡፡
ኢየሱስ ጌታ እንደ ሆነ በአፍህ ብትመሰክር እግዚአብሔርም ከሙታን እንዳስነሣው በልብህ ብታምን ትድናለህና፤ ሰው በልቡ አምኖ ይጸድቃልና በአፉም መስክሮ ይድናልና። ሮሜ 10፡9-10
ስለመዳንዎ አሁን እርግጠኛ መሆን ከፈለጉ ይህን ፀሎት ከልብዎ ይፀልዩ
እግዚአብሄር ሆይ ይህን የመዳኛ መንገድ በቃልህ ስለገለፅክልኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ እኔ ሃጢያተኛ እንደሆንኩ የሃጢያቴም ደሞዝ ለዘላለም ከእግዚአብሄር መለያየት መሆኑን አውቄያለሁ፡፡ እኔ የዘላለምን ሞትን እንዳልሞት ኢየሱስ በእኔ ምትክ የሃጢያቴን እዳ ሁሉ በመስቀል ላይ እንደከፈለ አምናለሁ፡፡ እግዚአብሄርን ከሙታን እንዳስነሳው አምናለሁ፡፡ ኢየሱስ በሞት ላይ ጌታ እንደሆነ እንዲሁም በህይወቴ ላይ ጌታ እንደሆነ እመሰክራለሁ፡፡ ልጅ አድርገህ ስለተቀበልከኝ አመሰግንሃለሁ፡፡ አሜን፡፡
ይህን ፅሁፍ ለሌሎች ሼር share ማድረግ ቢወዱ
ለተጨማሪ ፅሁፎች https://www.facebook.com/abiy.wakuma/notes
#ደህንነት #ዘላለም #መዳን #ፀጋ #ቤተክርስትያን #አማርኛ #ስብከት #ኢየሱስ #መፅሃፍቅዱስ #መንፈስቅዱስ #ህይወት #ፌስቡክ #አቢይዋቁማ #አቢይዋቁማዲንሳ